Skip to main content

Posts

Comparative Theology የነገረ መለኮት ንጽጽር (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት)/ በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሲኖዳ ሳልሳዊ

 የነገረ መለኮት ንጽጽር  (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት): የወደደ  ሁሉ በነጻ እንዲጠቀምበት ተፖስቷል። ይሁን እንጂ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ስለሆነ በየትኛውም መልኩ ለንግድ እንዲውል አልተፈቀድም። ልዩ ልዩ መግቢያ የሚለውን መጀመሪያ ካነበቡ በኋላ የተቀረውን በተመረጠው ቅደም ተከተል ማንበብ ይቻላል። ልዩ ልዩ መግቢያ   ጥምቀት   ትውፊት (ወግና ልማድ)   መካከለኝነት   ጾም የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ   ሥርዐት ንስሐ
Recent posts

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ (1)  ድንግል ማርያምን ስለማክበር (2) ለጥያቄዎች መልስ (ሀ) ድንግሊትን ‘የወይን ግንድ (ተክል)’ና የ ‘ሕይወት በር’ የሚል ማዕረግ  ለምን እንሰጣታለን? (ለ) ወደ ድንግል ማርያም መጸለይ ትክክል ነው ወይ? (3) የድንግል ማርያም ድንግልና ዘላለማዊነት (4) ለተቃራኒ አስተያየቶች መልስ (ሀ) “የመጀመሪያ ልጇን” የሚለው ሐረግ (ለ) “ሚስትህ” የሚለው ሐረግ (ሐ) “አብረው ከመሆናቸው በፊት ጸንሳ ተገኘች” (መ) “የመጀመሪያ ልጇን እስክትወልድ አላወቃትም” (ሠ)  “ወንድሞቹ” የሚለው ሐረግ   የቅድስት ድንግል ማርያም  ክብሯ (1) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ድንግል እመቤታችንን አያከብሩም፤ ደግሞም እንድታማልድላቸውም (እንድትማልድላቸውም)  አይጠይቋትም።ከእነርሱ ወገኖች አንዳንዶቹ እንዲያውም ጫጩቱ ከተፈለፈለ በኋላ ዋጋ ከሌለው የዶሮ እንቁላል ቅርፊት ጋር እስከሚያመሳስሏት ይደርሳሉ።ይህ የተጋነነ ማቃለል የመጣው ምናልባት ሮሜዋውያን ካቶሊኮች የተጋነነ ማክበር ስለሚያከብሯት ለዛ ተቃርኖ ከማሳየት አዝማሚያ ሊሆን ይችላል። ስለዚህም ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን አንዱንም የእርሷን በዓል አያከብሩም።  (2) አንዳንዶቹ የፕሮቴስታንት ወገኖች ድንግል ማርያምን “እህታችን” ይሏታል። (3) በተጨማሪ አንዳንዶቹ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጌታ ኢየሱስን በድንግልና ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር ጋብቻዋን ፈጽማለች፤ የ‘ኢየሱስ ወንድሞች’  ወይም የ’ጌታ ወንድሞች’ ተብለው የተጠሩ ልጆችን ወልዳለች ይላሉ።  (4) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ቤተክርስቲያናችን ለድንግል እመቤታችን የሰጠቻቸውን አንዳንድ የማዕረግ ስሞችም ይቃወማሉ።  (5) ድንግልን ያለማክበራቸው አንዱ...

ሥርዐት

ሥርዓቶች 1. የመስቀሉ አከባበር  2. ፊትን ወደ ምሥራቅ ስለማዞር    3. መቅደሱና መሠዊያው  4. ዕጣን    5. መብራትና ጧፍ    6. ሥዕሎችና ምስሎች (አርማዎች)    (1) መስቀሉን ማክበር በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት አማኞች መካከል ካሉት ልዩነቶች አንደኛው በኦርቶዶክስ ያለው አስደናቂ የመስቀል አከባበር ነው።ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ከመጸለያቸው በፊትም  ሆነ ከጸለዩ በኋላ “በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም” እያሉ  ራሳቸውን በመስቀሉ ምልክት አያማትቡም፣ ከመመገባቸው በፊትም በምግቡ ላይ የመስቀሉን ምልክት አያሳዩም። እንዲሁም ሰውንም ሆነ አልባሳትን  ለመባረክ በመስቀሉ ምልክት አይጠቀሙም። ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን መስቀሉን በልባቸው በማመናቸው ብቻ ሳይሠሩበት ረክተዋል። እስከቅርብ ጊዜ ድረስ መስቀልን በቤተክርስቲያናቸው ላይ ከፍ አድርገው (በቅርጽ ወይም በሥዕልም ቢሆን) አያሳዩምም ነበር። ብዙዎቹ መስቀሉን አያደርጉትም፤ አንዳቸውም መስቀሉን በእጃቸው አይዙም። የመስቀሉንም በዓላት አያከብሩም።  መስቀሉን በመያዝ እየዘመሩና እያወደሱ  ሰልፍን አያደርጉም። መስቀሉንም አይሳለሙም፤ በእርሱም በረከትን አይቀበሉም።  አሁን ኦርቶዶክስ ለምን ለመስቀሉ ትልቅ ሥፍራ እንደምትሰጥ፣ በመስቀሉ ማማተብ እርባናና ጥቅም ያለው እንዲሁም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርትን መሠረት ያደረገ መሆኑን ለማስረዳት እንሞክራለን።   (1) ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ አፅንኦት ማድረጉ  ጌታ አገልግሎቱን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በሚያስተምርበትም ጊዜ፣ ከስቅለቱም በፊት ለመስቀሉ ትልቅ አፅንኦት ሰጥቷል። እንዲህም አለ፦“...

መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ

መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ 1. ለድኅነትህ ከመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ይልቅ  የመንፈስ ፍሬዎች የበለጠ ጠቃሚ ናቸው 2. ስጦታዎች በአንተ ምስጉንነት የሚሰጡ አይደሉም፤ ስለዚህ ለእነዚህ ሽልማት የላቸውም 3. ስጦታዎቹ ይሰጣሉ ወይስ ይጠየቃሉ? 4. የጴንጤቆስጤ እንቅስቃሴና በልሳኖች የመናገር ስጦታ 5. በልሳን መናገር በስጦታዎቹ ቅደም ተከተል የመጨረሻው ነው 6. በልሳን መናገር የሁሉ ስጦታ አይደለም 7. በልሳን መናገር ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ መሆን አለበት 8. በልሳን መናገር መተርጎም አለበት 9. የ‘ራሱን ያንጻል’ ትርጕም ምንድነው? 10. ሐዋርያው በልሳን መናገርን በተመለከተ የሚደረግን ስህተት አጥብቆ ይዋጋል 11. በልሳን መናገር ለማያምኑ ምልክት ነው መንፈሳዊ ስጦታዎችና  በልሳኖች የመናገር ስጦታ ከፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን አንዳንዶቹ የመንፈስ ስጦታዎችን አጥብቀው ይይዛሉ። እንደ እግዚአብሔር ልጆችነታቸውና ወራሽነታቸው ልዩ መብታቸው አድርገው በማሰብ ሊያገኙትም ይጣጣራሉ። “ደግሞም ከሁሉ የሚበልጥ መንገድ አሳያችኋለሁ” (1 ቆሮ 12÷31) የሚለውን የጥቅሱን መጨረሻ አብረው ሳያገናዝቡ በፊታቸው “የሚበልጠውን የጸጋ ስጦታ በብርቱ ፈልጉ” (1 ቆሮ 12÷31) የሚለውን ጥቅስ ያኖራሉ።  በልሳን መናገርን እጅግ አስፈላጊ አድርገው ሲወስዱ ወዲያውኑ አስከትሎ ሐዋርያው ጳውሎስ “በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ” (1 ቆሮ 13÷1) በማለት የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ቸል ይሉታል። ሐዋርያው ከሁሉም ስጦታዎች ይልቅ ፍቅር እንዴት እንደሚመረጥ ያስረዳውን ይተዉታል። ለድኅነትህ ከመንፈስ ስጦታዎች ይልቅ የመንፈስ ፍሬ የበለጠ ...

ጾም

ጾም 1. አጽዋማት ሁሉ በሚስጥር የሚደረጉ ናቸውን? 2. የማኅበር ጾም   3. በተወሰኑ ጊዜያት መጾም 4. ለተቃውሞዎች መልስ  ● “ማንም አይፍረድባችሁ” ለሚለው ● አትክልት ብቻ የመብላት ጾም ለሚለው  ● ከተወሰኑ ምግቦች መከልከል ለሚለው 5. አምልኮን ስለ ማደራጀት የቤተ ክርስቲያን ሥልጣን ጾም በብሉይ ኪዳንም ሆነ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ጾም ምሳሌ ሳይሆን ትዕዛዝ እንደነበር እጅጉን ግልጽ ነው።ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጾምን ጨርሰው አይክዱም። በተግባር ግን ትተውታል ማለት ይቻላል። በዚህ ሥፍራ የጾም አስፈላጊነቱን፣ ጥቅሙን ፣ መንፈሳዊነቱን በአጠቃላይ መልኩ አልጽፍም። እነዚህ ሁሉ “የጾም መንፈሳዊነት” (“The spirituality of fasting”) በሚለው በሌላው መጽሐፋችን ሊነበቡ የሚችሉ ናቸው።  የልዩነት ነጥቦች (1) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጌታ በተራራው ስብከቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሠረት (ማቴ 6:17፣ 18) ጾም በእግዚአብሔርና በጿሚው መካከል በሚስጢር መደረግ አለበት ይላሉ። (2) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ለአማኞቻቸው ሁሉ የተወሰነ ቋሚ የጾም ቀን ወይም በመነሻ ምክንያት የሚደረግ ጾም የላቸውም።ነገር ግን ከጾማቸው አብዛኛው የየግል ልምምድ ነው። ይህም ግለሰቡ በፈለገው ቀን ወይም በፈለገው መልክ የሚያደርገው ነው።ቤተ ክርስቲያን በጿሚው ላይ ሥልጣን የላትም፣ ጣልቃም አትገባም።  (3) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን “እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ። እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች ጥላ ናቸውና፥ አካሉ ግን የክርስቶስ ነው።” (ቆላ 2÷16፣ 17) ለሚለው ሐረግ የስህተት ትርጉሙ ላይ ይመሠረታሉ። (4) ፕሮ...

መካከለኝነት

መካከለኛነት /ምልጃ 1. በክርስቶስ መካከለኛነት (አስታራቂነት)ና በቅዱሳን ምልጃ (አማላጅነት) መካከል ያለው ልዩነት 2. የቅዱሳኑ ምልጃ ለእኛ መጸለይ ብቻ ነው 3. እግዚአብሔር ሰዎች የጻድቅንን ምልጃ እንዲለምኑ ይጠይቃል   4. መላእክትና ቅዱሳን በምድር ላይ ያለንበትን ሁኔታ ያውቃሉን? 5. የቅዱሳኑ ታላቅነት፣ ዕውቀታቸውና አገልግሎታቸው 6. ስለ ቅዱሳን ታላቅነት ሌሎች ምሳሌዎች 7. በሞት የተለዩቱ ቅዱሳን አሁንም ቢሆን በሕይወት ናቸው 8. የመላእክት ምልጃ ምሳሌዎች  9. በጌታ ፊት የቅዱሳን ሞገስ  10. ተቃውሞዎችና ምላሾቻቸው  11. የቅዱሳንን ጸሎት መጠየቅ መንፈሳዊነቱ  12. ምልጃ በየዕለቱ የምናየው እውነታ ነው። ምልጃ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን የድንግል ማርያምን ወይም የመላእክትን ወይም የቅዱሳንን ምልጃ (አማላጅነት) አይቀበሉትም ። ለተቃውሞአቸውም መሠረቱ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ “ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው” (1 ዮሐ 2÷1) ና ሐዋርያው ጳውሎስ “እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው” (1 ጢሞ 2÷5) በማለት የጻፉት ነው።   (1)  በእርግጥ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መካከለኛነትና (አስታራቂነትና) በቅዱሳን ምልጃ (አማላጅነት) መካከል መሠረታዊ ልዩነት አለ  የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መካከለኛነት የ‘‘ማስተሰረይ’ ሥራ ነው፤ ያም ማለት በምትካችን ዕዳችንን የከፈለ ‘ማስተሰረያ’ ሆኖ የኃጢአትን ይቅርታ እንድናገኝ ያስታርቀናል ማለት...