Skip to main content

Posts

Comparative Theology የነገረ መለኮት ንጽጽር (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት)/ በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሲኖዳ ሳልሳዊ

 የነገረ መለኮት ንጽጽር  (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት): የወደደ  ሁሉ በነጻ እንዲጠቀምበት ተፖስቷል። ይሁን እንጂ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ስለሆነ በየትኛውም መልኩ ለንግድ እንዲውል አልተፈቀድም። ልዩ ልዩ መግቢያ የሚለውን መጀመሪያ ካነበቡ በኋላ የተቀረውን በተመረጠው ቅደም ተከተል ማንበብ ይቻላል። ልዩ ልዩ መግቢያ   ጥምቀት   ትውፊት (ወግና ልማድ)   መካከለኝነት   ጾም የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ   ሥርዐት ንስሐ
Recent posts

ከቄስ ( ዶ/ር ) ቶሎሳ ይልቅ

 አድማጭ ተመልካቾቼ አንደምን ከረማችሁ? የአብርሃም አምላክና አምላካችን የተመሰገነ ይሁንና እኔ ደህና ነኝ።"ከቄስ (ዶ/ር ) ቶሎሳ ይልቅ" በሚል ርዕስ ያዘጋጀሁትን  የሚከተለውን መልዕክቴን እንድትከታተሉልኝ በታላቅ አክብሮት እጋብዛችኋለሁ። ባንቱ ገብረማርያም ነኝ ከቄስ (ዶ/ር) ቶሎሳ ይልቅ           ቄስ (ፓስተር) ዶ/ር ቶሎሳ  ጉዲና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን በአትላንታ/ጆርጂያ ፓስተር መሆናቸው በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅ ይመስለኛል። በበኩሌ የማከብራቸውም ሰው ናቸው። በወንጌላውያን መኻል ለበርካታ ዐመታት ለኢትዮጵያ ሰላምና አንድነት የተናገሩ፣ ያሳሰቡና የጸለዩ መሆናቸውን ሰምቼአለሁ።በነገዳቸው የተደራጁትን የወንዛቸው ልጆችን ወቀሳ ተቋቁመው ለመላው ኢትዮጵያዊ ሲጮኹ የኖሩ ናቸው።           ስለ እሬቻ የሰጡት ትምህርት እስከዛሬ እንደሞዴል የማየው ነው። እሬቻን እንዳይከተሉና እንዳያስፋፉ የአሁኖቹን የመንግሥት ዐላፊዎች የመከሩበትንም ጊዜ አስታውሳለሁ።           የወንጌላውያን ሽማግሌ ብቻ ሳይሆኑ በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ የአገር ሽማግሌ አድርጌ አያቸዋለሁ። ይህን መደላድል የማስቀምጠው ስለእርሳቸው ያለኝን አስተያየት ለማስታወቅና ይኸው ሐሳቤ የጸና መሆኑን ለማስጮህ ነው።አስተያየቴን አልጠየቁኝም፣ የሚጨምርላቸውም ሆነ የሚቀንስባቸው ነገር እንደማይኖርም ጠንቅቄ አውቃለሁ። መደላድሉን አስቀድሜ  ማስቀመጤ ወንድሞችንና እህቶችን “አይዟችሁ አትደንግጡ” ለማለት ያህል ነው። ...

አንበሶቼ! አጠፋሁ እንዴ?

  Click the link https://amharic.borkena.com/2025/07/07/%e1%8a%a0%e1%8a%95%e1%89%a0%e1%88%b6%e1%89%bc%e1%8a%a0%e1%8c%a0%e1%8d%89-%e1%8a%a5%e1%8a%95%e1%8b%b4-%e1%89%a0%e1%89%a3%e1%8a%95%e1%89%b1-%e1%8c%88%e1%89%a5%e1%88%a8%e1%88%9b%e1%88%ad/?fbclid=IwY2xjawLb4NtleHRuA2FlbQIxMQABHsL6Gqmqtz2ag0uohgL7TZEUkHOicXNezkQlnYAUtu23TIi1bPcVM8_JyJ3N_aem_RcmtzE8ApbTC_WDA7IgHxA

ደግሞ ባንዳ/ ሆዳም በሉኝ አሉ!

 ደግሞ ባንዳ /ሆዳም በሉኝ አሉ!  ማህበራዊ አንቂ አይደለሁም። ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ግን ተቆርቋሪ ነኝ። እንዳውም ለዘለቄታው ይጠቀምበታል ያልኩትና  እያስተዋወቅሁት ያለ  የራሴ ዐሳብ  አለኝ።  በመቀጠል የምጽፈው ስለ ዐማራና ዎገኖቹ ነው። ዐማራ ነኝና። ስለ ሌሎች ነገዶችና ጎሳዎች የሚፈቀድልኝ ስላልመሰለኝ  አልጽፍም። ታዲያ ባንጠቀምባቸው ወይም እጅግ በተመጠነ ልክ ብቻ ብንጠቀምባቸው የምላቸው ሁለት ቃላት (ከእነርሱ ተቀራራቢ የሆኑቱን ሁሉ ማለቴ ነው) አሉ። እነርሱም  “ባንዳ” ና “ሆዳም“ የሚሉት ናቸው።የምጽፈው እነርሱን የታከከ ነገር ነው።      ከጠላት ጋር በማበራቸው ምክንያት በታሪክ ባንዳ ተብለው የሚጠሩ መኖራቸውን አላጣሁትም። የወገኑን ነጻነት የማረጋገጥ ሥራን አሳንሶ፣ የአጭር ጊዜ የግል ጥቅም ማግኘትን አግዝፎ መያዝና ለተጋድሎው እንቅፋት መሆን ሆዳም ሊያሰኝ እንደሚችልም እረዳለሁ።ስንጠቀምባቸው ምናልባት በዚህ እሳቤ ቃኝተን እንደሆነም እገምታለሁ። ይሁን እንጂ አንድ ዎገን በዐሳብ ሊለይ ይችላል።ተቀባይነት ያለውን ዐሳቡን ተቀባይነት ወደ ሌለው ሊለውጥም ይችላል። ተቃራኒ የሆነ ዐሳቡን ትቶ የሚቃረነውን ዐሳብ ሊቀበል ይችላል። በርካታ ሰው  “ዐማራ” ነኝ የሚለውን ማንነት ለማስታወስ ወይም ለመቀበል እንኳ ምን ያህል ጊዜ እንደፈጀበት ልብ ይሏል። ሁሉም የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ በአንድ ጊዜ በአንድ መስመር ላይ ይገኛል ለማለት ትልቅ ድፍረትን ይጠይቃል። ስለዚህ የራስን ዎገን እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ አድርጎ ባንዳ/ሆዳም እያሉ ፈርጆ ስብዕናውን መግደል - ባንዳ በሚለውና በሚባለው መኻል ያለውን ልዩነት ያሳይ እንደሆነ እንጂ - ለዐማራው ምን ይጠቅመዋል? በተ...

ንቄው ነበር

 ንቄው ነበር! የገጠመኝን ታሪክ ላውጋችሁ። ከ30 ዓመት በፊት የሆነ  ነው። የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ሦስት ወጣት ፍልስጤማውያን ነበሩ። ከአንደኛው ጋር እንዳውም አንድ ሪደር  (ፕሮፌሰር) ነበረን።ታዲያ ወንድማቸው ስለሆነው የአይሁድ ሕዝብ ባወራን ጊዜ  <<ልታስተናግደው መኝታ ቤት የሰጠኸው ሰው ቤትህን ሲቀማህ ዝም ብለህ ታየዋለህ እንዴ? እኛም አይሁዶችን የምናያቸው እንደዛ ነው። ምኞታችን ሁሉ ትምህርታችንን  ጨርሰን እነርሱን መውጋት ነው >>  ብለውኝ ነበር።  የተላኩ(ህ)በትን ትምህርት እንደምንም ጨርሼ ትምህርት ቤቱን ከተለየሁ ወዲህ ግንኙነት ስለሌን ያድርጉት ፥ አያድርጉት አላውቅም። ሁላችንም “የሰው አገር ሰው” መሆናችን አቆራኝቶን ነበርና በጊዜው ግን እንቀራረብ ነበር።ታዲያ ከዕለታት አንዱን ቀን፥  የጾም ፍቺያቸው ጊዜ ይመስለኛል (አሁን ተዘንግቶኛል) ልጎበኛቸው እቤታቸው ሄድኩ። አንድ “የታላቁን የዐረብ ኢምፓየር”  ካርታ እስቲከር  በቤታቸው ግድግዳና በብዙ ሥፍራ ተለጥፎ አየሁ።ተገረምኩም። ኢትዮጵያ ጭምር “የአፍሪካ ቀንድ” አገሮች በዚያ ካርታ ተጨምረው ነበርና።  <<ይህ ደግሞ ምንድነው? ኢትዮጵያ እዚህ ውስጥ እንዴት ተጨመረች?>>  ብዬ ጠየቅኋቸው።ተደናገጡ። ሊያስረዱኝም ሞከሩ።  <<የነቢያችን ተከታዮች ዐበሻ አገር በተጠለሉ ጊዜ ነጋሻቸው ሙስሊም ሆኖ ነበር>>  አሉኝ። ሆኖም ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያን በዐረብ አገር ለማካተት  ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አልታየኝም። አፈጣጠራቸውም ታሪካችውም ለየቅል ነውና።ይሁን እንጅ አልተንጨረጨርኩም።  <<ምንም አይደለም፥ ይህን...

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ (1)  ድንግል ማርያምን ስለማክበር (2) ለጥያቄዎች መልስ (ሀ) ድንግሊትን ‘የወይን ግንድ (ተክል)’ና የ ‘ሕይወት በር’ የሚል ማዕረግ  ለምን እንሰጣታለን? (ለ) ወደ ድንግል ማርያም መጸለይ ትክክል ነው ወይ? (3) የድንግል ማርያም ድንግልና ዘላለማዊነት (4) ለተቃራኒ አስተያየቶች መልስ (ሀ) “የመጀመሪያ ልጇን” የሚለው ሐረግ (ለ) “ሚስትህ” የሚለው ሐረግ (ሐ) “አብረው ከመሆናቸው በፊት ጸንሳ ተገኘች” (መ) “የመጀመሪያ ልጇን እስክትወልድ አላወቃትም” (ሠ)  “ወንድሞቹ” የሚለው ሐረግ   የቅድስት ድንግል ማርያም  ክብሯ (1) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ድንግል እመቤታችንን አያከብሩም፤ ደግሞም እንድታማልድላቸውም (እንድትማልድላቸውም)  አይጠይቋትም።ከእነርሱ ወገኖች አንዳንዶቹ እንዲያውም ጫጩቱ ከተፈለፈለ በኋላ ዋጋ ከሌለው የዶሮ እንቁላል ቅርፊት ጋር እስከሚያመሳስሏት ይደርሳሉ።ይህ የተጋነነ ማቃለል የመጣው ምናልባት ሮሜዋውያን ካቶሊኮች የተጋነነ ማክበር ስለሚያከብሯት ለዛ ተቃርኖ ከማሳየት አዝማሚያ ሊሆን ይችላል። ስለዚህም ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን አንዱንም የእርሷን በዓል አያከብሩም።  (2) አንዳንዶቹ የፕሮቴስታንት ወገኖች ድንግል ማርያምን “እህታችን” ይሏታል። (3) በተጨማሪ አንዳንዶቹ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጌታ ኢየሱስን በድንግልና ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር ጋብቻዋን ፈጽማለች፤ የ‘ኢየሱስ ወንድሞች’  ወይም የ’ጌታ ወንድሞች’ ተብለው የተጠሩ ልጆችን ወልዳለች ይላሉ።  (4) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ቤተክርስቲያናችን ለድንግል እመቤታችን የሰጠቻቸውን አንዳንድ የማዕረግ ስሞችም ይቃወማሉ።  (5) ድንግልን ያለማክበራቸው አንዱ...

ሥርዐት

ሥርዓቶች 1. የመስቀሉ አከባበር  2. ፊትን ወደ ምሥራቅ ስለማዞር    3. መቅደሱና መሠዊያው  4. ዕጣን    5. መብራትና ጧፍ    6. ሥዕሎችና ምስሎች (አርማዎች)    (1) መስቀሉን ማክበር በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት አማኞች መካከል ካሉት ልዩነቶች አንደኛው በኦርቶዶክስ ያለው አስደናቂ የመስቀል አከባበር ነው።ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ከመጸለያቸው በፊትም  ሆነ ከጸለዩ በኋላ “በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም” እያሉ  ራሳቸውን በመስቀሉ ምልክት አያማትቡም፣ ከመመገባቸው በፊትም በምግቡ ላይ የመስቀሉን ምልክት አያሳዩም። እንዲሁም ሰውንም ሆነ አልባሳትን  ለመባረክ በመስቀሉ ምልክት አይጠቀሙም። ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን መስቀሉን በልባቸው በማመናቸው ብቻ ሳይሠሩበት ረክተዋል። እስከቅርብ ጊዜ ድረስ መስቀልን በቤተክርስቲያናቸው ላይ ከፍ አድርገው (በቅርጽ ወይም በሥዕልም ቢሆን) አያሳዩምም ነበር። ብዙዎቹ መስቀሉን አያደርጉትም፤ አንዳቸውም መስቀሉን በእጃቸው አይዙም። የመስቀሉንም በዓላት አያከብሩም።  መስቀሉን በመያዝ እየዘመሩና እያወደሱ  ሰልፍን አያደርጉም። መስቀሉንም አይሳለሙም፤ በእርሱም በረከትን አይቀበሉም።  አሁን ኦርቶዶክስ ለምን ለመስቀሉ ትልቅ ሥፍራ እንደምትሰጥ፣ በመስቀሉ ማማተብ እርባናና ጥቅም ያለው እንዲሁም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርትን መሠረት ያደረገ መሆኑን ለማስረዳት እንሞክራለን።   (1) ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ አፅንኦት ማድረጉ  ጌታ አገልግሎቱን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በሚያስተምርበትም ጊዜ፣ ከስቅለቱም በፊት ለመስቀሉ ትልቅ አፅንኦት ሰጥቷል። እንዲህም አለ፦“...