ካውንስሉ ካስገደደው የሚስተካከል የጸሎት ጥያቄ ባይሆንም፦ እነዚያ ሁሉ አባቶች ፣ የቤተክርስቲያን መሬዎችና፣ አዋቂዎች መክረው (ግራና ቀኙን አይተው) በካውንስሉ በኩል ካቀረቡት አስገዳጅ የጸሎት ጥያቄ የተሻለ አቅርቤአለሁ አልልም። ይሁን እንጂ የአደባባዩ ቢቀር የተሰማችሁ በየግላችሁ ብትጸልዩበት ይሆናል።በተባለው የሰላም መልዕክትና ጸሎት ጊዜም ልታስቡት ትችላላችሁ። “በአዲስ አበባ ያላችሁ ወንጌላውያን ተረጋጉ” በሚለው ጽሑፌ ያቀረብኩት የጸሎት ጥያቄ ነበር። ፋኖዎች የሃይማኖት እኩልነትን የማክበር አቋማቸውን በተግባር ማሳየት እንዲችሉ እግዚአብሔር አምላክ እንዲረዳቸው ለፋኖ መነሳት ምክንያት የሆነው የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ መጨፍጨፍና መፈናቀል ስለሆነ እግዚአብሔር ዐማራውንና ዎገኖቹን እንዲታደግ ፥ ሊከፋፍሉትና ሊያጠፋት ሌት ተቀን የሚያደቡትን ምክራቸውን እንዲያፈርስ ፥ ኅይላቸውንም እንዲበትን ከኦርቶዶክሳውያን ጋር በበጎ ዐይን ለመተያየት እንዲያበቃንና ወንጌልን በመተባበር ወደ መዝራቱ በተለይ ዕዳሪ መሬት ወደ ማውጣቱ ልቦቻችንን እንዲያዘነብል የብልጽግና የበላይነት ለረዠም ጊዜ ከቀጠለ ኢትዮጵያ ወደ አረማዊ አገርነት የመገስገስ አደጋ ስለሚገጥማት ከዚያ እንዲታደጋት። እኛም ከኦርቶዶክሳውያኑ ጋር ሆነን ኢትዮጵያን ከዚያ ለማትረፍ በመሥራቱ እንዲያተጋን እንጸልይ