Skip to main content

Posts

Showing posts from August, 2023

ለምን ትጮህብኛለህ ?

ለ ምን ትጮህብኛለህ?     አሁን ብዙም አልቆየሁም። ዳላስ በቶሎ ተመልሼአለሁ። በዛሬው የዳላስ ቆይታዬ በላፕቶፔ ላይ አንዳንድ ነገሮችን ለመሥራት ካረፍኩበት ቤት አቅራቢያ ካለ አንድ ስታርበክስ ተገኝቼአለሁ። ታዲያ ሌላ ጊዜ ስታርበክስ ስቀመጥ ልብ ያላልኩትን አንድ  ነ ገር በዚያ ልብ አልኩኝ። ለካ ‘ስታርበክስ’ የማይመጣ የሰው ዘር ዐይነት የለም። ይመጣል፥ቡናውን ያዛል፥ይዞ ይወጣል። ወይም እንደኔው ሊጠጣ ይቀመጣል።ሌላም ይመጣል ፣ እንዲሁ፤  አያቋርጥም። ኢትዮጵያኖቹን ጨምሮ ላቲኖዎች ፥ የሩቅ ምሥራቅ ዝርያዎች ፥ ነጮች፥ አልፎ አልፎ ጥቁሮችና የመኻከለኛው ኤስያ ሰዎች ሁሉ ይመጣሉ።   እዚህ ስታርበክስ ተቀምጠው ቡናቸውን ከሚጠጡት መኻል የኢትዮጵያውያንና የሩቅ ኤስያ ሰውን የሚመስል መልክ ያላቸው ይበዛሉ። በየቦታው ፈንጠርጠር ብለው በግል ላፕቶፖቻቸው የሚሠሩ፣ “ጥበበኛውን ስልካቸውን” በሚገባው ቋንቋ የሚያነጋገሩ ያታያሉ ።   ልማዳቸው ነው መሰለኝ የሩቅ ምሥራቅ ሰው መልክ ካላቸው  ሰብሰብ ብለው ካርታ የሚጫወቱም አሉ። ሳንቲም ሲያወጡ ስላላየሁ ቁማር አይመስለኝም። ጊዜ ማሳለፊያ ነው። የሚያልፍ ጊዜ በአሜሪካ ማግኘታቸው ያስደንቃል! አይደል? የእኛ ሰው ግን  በጠረጴዛ ዙሪያ ተኮልኩሎ ያወጋል። በትግርኛ ወይም በኦሮምኛ የሚናገረው ተቀምጦ ሲያወራ  አልሰማሁም ። የሚያዘውን አዝዞ ይዞ  ውልቅ ነው የሚለው። ይህን የለየሁት በስልክ ከሚያወራው በሰማሁት ነው። ጠረጴዛውን ከብበው ሲያወሩ የማየውና እየሰማሁ ያለሁት  አማርኛ ተናጋሪዎቹን ነው። ወሬያቸውም  “ ቦለቲካ” ነው።  «አይ የእኛ ነገር ይገርማል!ሁሌ ቦለቲካ! መቼ ይሆን የምንገላገ...

ጦርነትም ጊዜ አለው?

  ጦርነትም ጊዜ አለው? በእኔ ላይ የእናቴ ተጽዕኖ እጅግ ከባድ ነው። ከ”ነገሩ ጦም እደሩ” ትለኝ ነበር እንጂ ፤ እንደ አንዳንድ ወላጆች “ተደብድበህ እንዳትገባ” አትለኝም ነበር። ለዚህ ነው ወታደር መሆን በሚደነቅበትና መሆን  በተለመደበት ማኅበረሰብ ባድግም፣ ወታደር የመሆን ፍላጎት ኖሮኝ የማያውቀው።ሙሉ ሰው ከሆንኩም በኋላ ዐሳቤ በወንጌል አገልግሎት ላይ ስለነበርና ይኼም የሚደረገው ስደትን ተቋቁሞ እጅን በማንም ላይ በአለማንሳት ነው ብዬ አምን ስለነበር ከጦረኝነት ዐሳብ ርቄ የኖርኩ ነኝ። ዛሬ ላይ ግን የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ መንግሥት አልጠበቀኝም፣ እንዳውም በስቃዬ እየተሳለቀብኝ ነው፥  ከእንግዲህ ወዲያ ተዘቅዝቄ አልሰቀልም ፥ እንደ እንስሳ አልታረድም፥ ቆዳዬ  አይገፈፍም፥ የአካል ክፍሌ በአዋዜ እየተወራረደ አይበላም፥ እህቴም እናቴም አትደፈርም፥ ጡቷም አይቆረጥም፥  እርጉዝ  እህቴ በስለት ተቀዳ ጽንሷ አይጣልም፥  ህጻኗ  እህቴ “ወላሂ ዳግመኛ ዐማራ አልሆንም አትግደሉኝ” ብላ አትለምንም፥ አልገደልም፥ በውርደትም አልቀበርም፥ አልፈናቀልም፥ አልዘረፍም በማለት  በአልሞት ባይ ተጋዳይነት (በተከላካይነት) ጦር ቢመዝ የማከላክል አልሆንም። እንዳውም ይኸንን  ለማድረግ ወስኖ ደግፈኝ ቢለኝ (ጡረተኛ ብሆንም እንኳ) በምችለው ከመደገፍ ወደኋላ አልልም። የማወራው ስለ ድል አይደለም። ድሉ ለእግዚአብሔር የሚተው ነው። ነገር ግን ሕልውናንና ነጻነትን ማጣትን እምቢ ስለማለት ነው። ከማኅበራዊ መገናኛዎች እንደምከታተለው ደግሞ የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ዛሬ ይኸንኑ ለማድረግ  ፋኖ ሆኖ  ወጥቷል። አበጀህ፣ እግዚአብሔር ይርዳህ  ብዬአለሁ። ግልጽ ላድርገው- መከላከሉን ነው- ...