Skip to main content

Posts

Showing posts from August, 2023

ጦርነትም ጊዜ አለው?

  ጦርነትም ጊዜ አለው? በእኔ ላይ የእናቴ ተጽዕኖ እጅግ ከባድ ነው። ከ”ነገሩ ጦም እደሩ” ትለኝ ነበር እንጂ ፤ እንደ አንዳንድ ወላጆች “ተደብድበህ እንዳትገባ” አትለኝም ነበር። ለዚህ ነው ወታደር መሆን በሚደነቅበትና መሆን  በተለመደበት ማኅበረሰብ ባድግም፣ ወታደር የመሆን ፍላጎት ኖሮኝ የማያውቀው።ሙሉ ሰው ከሆንኩም በኋላ ዐሳቤ በወንጌል አገልግሎት ላይ ስለነበርና ይኼም የሚደረገው ስደትን ተቋቁሞ እጅን በማንም ላይ በአለማንሳት ነው ብዬ አምን ስለነበር ከጦረኝነት ዐሳብ ርቄ የኖርኩ ነኝ። ዛሬ ላይ ግን የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ መንግሥት አልጠበቀኝም፣ እንዳውም በስቃዬ እየተሳለቀብኝ ነው፥  ከእንግዲህ ወዲያ ተዘቅዝቄ አልሰቀልም ፥ እንደ እንስሳ አልታረድም፥ ቆዳዬ  አይገፈፍም፥ የአካል ክፍሌ በአዋዜ እየተወራረደ አይበላም፥ እህቴም እናቴም አትደፈርም፥ ጡቷም አይቆረጥም፥  እርጉዝ  እህቴ በስለት ተቀዳ ጽንሷ አይጣልም፥  ህጻኗ  እህቴ “ወላሂ ዳግመኛ ዐማራ አልሆንም አትግደሉኝ” ብላ አትለምንም፥ አልገደልም፥ በውርደትም አልቀበርም፥ አልፈናቀልም፥ አልዘረፍም በማለት  በአልሞት ባይ ተጋዳይነት (በተከላካይነት) ጦር ቢመዝ የማከላክል አልሆንም። እንዳውም ይኸንን  ለማድረግ ወስኖ ደግፈኝ ቢለኝ (ጡረተኛ ብሆንም እንኳ) በምችለው ከመደገፍ ወደኋላ አልልም። የማወራው ስለ ድል አይደለም። ድሉ ለእግዚአብሔር የሚተው ነው። ነገር ግን ሕልውናንና ነጻነትን ማጣትን እምቢ ስለማለት ነው። ከማኅበራዊ መገናኛዎች እንደምከታተለው ደግሞ የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ዛሬ ይኸንኑ ለማድረግ  ፋኖ ሆኖ  ወጥቷል። አበጀህ፣ እግዚአብሔር ይርዳህ  ብዬአለሁ። ግልጽ ላድርገው- መከላከሉን ነው- ...