Skip to main content

Posts

Showing posts from December, 2023

ፋኖ ያሸንፍ

ፋኖ ያሸንፍ! ባለፈው ጊዜ “ፋኖ እንዲያሸንፍ ለምን እንደምመኝ /እንደምፈልግ ጊዜ ካገኘሁ እጽፍበታለሁ ፤ እስከዚያው ግን ምኞቴ እንዲደርስ መርቁኝ “ ብዬአችሁ ነበር።  በአጭሩ፦ፋኖ እንዲያሸንፍ መመኘቴ “አንቺም ትሞቺብኝ ይሆን ወይ? (እንደ ተረቱ)” በሚባል አስተዳደር ላይ የተጠረቀመውን መዝጊያ ወለል  አድርጎ ይከፍታል” በሚል እሳቤ ነው። ("አንቺም ትሞችብኝ ይሆን ወይ" ማለት እንዲወድቅ የማይፈለግ ቅን መንግሥት ለማለት ነው። ተረቱን ለማወቅ የሚፈልግ በአስተያየት መስጪያ ላይ ይጠይቅ) እንደሚታወቀው የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ከበዳዮቹና ከአስጨናቂዎቹ ይታደጉት ዘንድ በቅርቦቹ አሥርት ዐመታት በኢትዮጵያ ለተነሱት መንግሥታት አቤቱታውን ሲያሰማቸው ኖሯል። ሰላማዊ በተባለ መንገድ ጥያቄውን አቅርቦላቸዋል። ይሁን እንጂ ሊከላከልለት የፈቀደ የመንግሥት አካል ብቅ አላለም። በችግሩ አላዘኑለትም። ያም ቀርቶ መሳለቂያ ባላደረጉት  ምንኛ መልካም በሆነ ነበር።  እንዳውም አሁን በመጨረሻ  በብዙ ሥጋት ውስጥ እያለ መንግሥት ራሱ “ወርሰህ ታጠቅ” ያለውን ጠመንጃ አስረክብ ብሎ ተነሳበት። ሌሎቹ ሳይነኩ ልዩ ኅይሉንም አፈረሰበት።ጦርም አዘመተበት።የዐማራ ሕዝብ ምን ምርጫ ነበረው? ምን ቀረው? የመከላከል ጦርነት ውስጥ ገባ። ለተጋድሎው ፋኖ ዐይነተኛ መሪው ሆኖ ብቅ አለ።እግዚአብሔር የዐማራን ሕዝብና ዎገኖቹን  ሊያስበው መጀመሩ ነው መሰለኝ ሁኔታዎች ተገጣጠሙና ፋኖ የዐማራን ሕዝብና ዎገኖቹን የሚወጉትን ኃይላት የሚገዳደር ኅይል ሆኖ ወጣ።ታዲያ በዚህ እራስን  የማዳን ጦርነቱ ነው ፋኖ እንዲያሸንፍ የፈለግሁት/የተመኘሁት።የአብርሃም አምላክና አምላክህ ይርዳህ ! ድሉን ይስጥህ ብዬዋለሁ።  ተሳስቼ ሊሆን ይችላል። ስ...