Skip to main content

Posts

Showing posts from June, 2025

ደግሞ ባንዳ/ ሆዳም በሉኝ አሉ!

 ደግሞ ባንዳ /ሆዳም በሉኝ አሉ!  ማህበራዊ አንቂ አይደለሁም። ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ግን ተቆርቋሪ ነኝ። እንዳውም ለዘለቄታው ይጠቀምበታል ያልኩትና  እያስተዋወቅሁት ያለ  የራሴ ዐሳብ  አለኝ።  በመቀጠል የምጽፈው ስለ ዐማራና ዎገኖቹ ነው። ዐማራ ነኝና። ስለ ሌሎች ነገዶችና ጎሳዎች የሚፈቀድልኝ ስላልመሰለኝ  አልጽፍም። ታዲያ ባንጠቀምባቸው ወይም እጅግ በተመጠነ ልክ ብቻ ብንጠቀምባቸው የምላቸው ሁለት ቃላት (ከእነርሱ ተቀራራቢ የሆኑቱን ሁሉ ማለቴ ነው) አሉ። እነርሱም  “ባንዳ” ና “ሆዳም“ የሚሉት ናቸው።የምጽፈው እነርሱን የታከከ ነገር ነው።      ከጠላት ጋር በማበራቸው ምክንያት በታሪክ ባንዳ ተብለው የሚጠሩ መኖራቸውን አላጣሁትም። የወገኑን ነጻነት የማረጋገጥ ሥራን አሳንሶ፣ የአጭር ጊዜ የግል ጥቅም ማግኘትን አግዝፎ መያዝና ለተጋድሎው እንቅፋት መሆን ሆዳም ሊያሰኝ እንደሚችልም እረዳለሁ።ስንጠቀምባቸው ምናልባት በዚህ እሳቤ ቃኝተን እንደሆነም እገምታለሁ። ይሁን እንጂ አንድ ዎገን በዐሳብ ሊለይ ይችላል።ተቀባይነት ያለውን ዐሳቡን ተቀባይነት ወደ ሌለው ሊለውጥም ይችላል። ተቃራኒ የሆነ ዐሳቡን ትቶ የሚቃረነውን ዐሳብ ሊቀበል ይችላል። በርካታ ሰው  “ዐማራ” ነኝ የሚለውን ማንነት ለማስታወስ ወይም ለመቀበል እንኳ ምን ያህል ጊዜ እንደፈጀበት ልብ ይሏል። ሁሉም የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ በአንድ ጊዜ በአንድ መስመር ላይ ይገኛል ለማለት ትልቅ ድፍረትን ይጠይቃል። ስለዚህ የራስን ዎገን እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ አድርጎ ባንዳ/ሆዳም እያሉ ፈርጆ ስብዕናውን መግደል - ባንዳ በሚለውና በሚባለው መኻል ያለውን ልዩነት ያሳይ እንደሆነ እንጂ - ለዐማራው ምን ይጠቅመዋል? በተ...

ንቄው ነበር

 ንቄው ነበር! የገጠመኝን ታሪክ ላውጋችሁ። ከ30 ዓመት በፊት የሆነ  ነው። የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ሦስት ወጣት ፍልስጤማውያን ነበሩ። ከአንደኛው ጋር እንዳውም አንድ ሪደር  (ፕሮፌሰር) ነበረን።ታዲያ ወንድማቸው ስለሆነው የአይሁድ ሕዝብ ባወራን ጊዜ  <<ልታስተናግደው መኝታ ቤት የሰጠኸው ሰው ቤትህን ሲቀማህ ዝም ብለህ ታየዋለህ እንዴ? እኛም አይሁዶችን የምናያቸው እንደዛ ነው። ምኞታችን ሁሉ ትምህርታችንን  ጨርሰን እነርሱን መውጋት ነው >>  ብለውኝ ነበር።  የተላኩ(ህ)በትን ትምህርት እንደምንም ጨርሼ ትምህርት ቤቱን ከተለየሁ ወዲህ ግንኙነት ስለሌን ያድርጉት ፥ አያድርጉት አላውቅም። ሁላችንም “የሰው አገር ሰው” መሆናችን አቆራኝቶን ነበርና በጊዜው ግን እንቀራረብ ነበር።ታዲያ ከዕለታት አንዱን ቀን፥  የጾም ፍቺያቸው ጊዜ ይመስለኛል (አሁን ተዘንግቶኛል) ልጎበኛቸው እቤታቸው ሄድኩ። አንድ “የታላቁን የዐረብ ኢምፓየር”  ካርታ እስቲከር  በቤታቸው ግድግዳና በብዙ ሥፍራ ተለጥፎ አየሁ።ተገረምኩም። ኢትዮጵያ ጭምር “የአፍሪካ ቀንድ” አገሮች በዚያ ካርታ ተጨምረው ነበርና።  <<ይህ ደግሞ ምንድነው? ኢትዮጵያ እዚህ ውስጥ እንዴት ተጨመረች?>>  ብዬ ጠየቅኋቸው።ተደናገጡ። ሊያስረዱኝም ሞከሩ።  <<የነቢያችን ተከታዮች ዐበሻ አገር በተጠለሉ ጊዜ ነጋሻቸው ሙስሊም ሆኖ ነበር>>  አሉኝ። ሆኖም ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያን በዐረብ አገር ለማካተት  ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አልታየኝም። አፈጣጠራቸውም ታሪካችውም ለየቅል ነውና።ይሁን እንጅ አልተንጨረጨርኩም።  <<ምንም አይደለም፥ ይህን...