Skip to main content

ደግሞ ባንዳ/ ሆዳም በሉኝ አሉ!

 ደግሞ ባንዳ /ሆዳም በሉኝ አሉ! 

ማህበራዊ አንቂ አይደለሁም። ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ግን ተቆርቋሪ ነኝ። እንዳውም ለዘለቄታው ይጠቀምበታል ያልኩትና  እያስተዋወቅሁት ያለ  የራሴ ዐሳብ  አለኝ።  በመቀጠል የምጽፈው ስለ ዐማራና ዎገኖቹ ነው። ዐማራ ነኝና። ስለ ሌሎች ነገዶችና ጎሳዎች የሚፈቀድልኝ ስላልመሰለኝ  አልጽፍም። ታዲያ ባንጠቀምባቸው ወይም እጅግ በተመጠነ ልክ ብቻ ብንጠቀምባቸው የምላቸው ሁለት ቃላት (ከእነርሱ ተቀራራቢ የሆኑቱን ሁሉ ማለቴ ነው) አሉ። እነርሱም  “ባንዳ” ና “ሆዳም“ የሚሉት ናቸው።የምጽፈው እነርሱን የታከከ ነገር ነው።

    ከጠላት ጋር በማበራቸው ምክንያት በታሪክ ባንዳ ተብለው የሚጠሩ መኖራቸውን አላጣሁትም። የወገኑን ነጻነት የማረጋገጥ ሥራን አሳንሶ፣ የአጭር ጊዜ የግል ጥቅም ማግኘትን አግዝፎ መያዝና ለተጋድሎው እንቅፋት መሆን ሆዳም ሊያሰኝ እንደሚችልም እረዳለሁ።ስንጠቀምባቸው ምናልባት በዚህ እሳቤ ቃኝተን እንደሆነም እገምታለሁ።

ይሁን እንጂ አንድ ዎገን በዐሳብ ሊለይ ይችላል።ተቀባይነት ያለውን ዐሳቡን ተቀባይነት ወደ ሌለው ሊለውጥም ይችላል። ተቃራኒ የሆነ ዐሳቡን ትቶ የሚቃረነውን ዐሳብ ሊቀበል ይችላል። በርካታ ሰው  “ዐማራ” ነኝ የሚለውን ማንነት ለማስታወስ ወይም ለመቀበል እንኳ ምን ያህል ጊዜ እንደፈጀበት ልብ ይሏል። ሁሉም የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ በአንድ ጊዜ በአንድ መስመር ላይ ይገኛል ለማለት ትልቅ ድፍረትን ይጠይቃል። ስለዚህ የራስን ዎገን እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ አድርጎ ባንዳ/ሆዳም እያሉ ፈርጆ ስብዕናውን መግደል - ባንዳ በሚለውና በሚባለው መኻል ያለውን ልዩነት ያሳይ እንደሆነ እንጂ - ለዐማራው ምን ይጠቅመዋል? በተለይም በሰፊው የዐማራ ሕዝብ በመሪነት የመመረጥ ውድድር በሌለበት ሁኔታ።  

የሚፈለገውን ነገር ማሳየት አይበቃም ወይ? ባንድ/ሆዳም ከማለት ይልቅ ሌሎች ቃላትን መጠቀም ቢመረጥ እላለሁ።

ለምሳሌ፦ ዐሳቡ ወይም ሥራው እየተጨመረ፦

  • “ለጊዜው ከእኔ ዐሳብ በተቃራኒ የቆምከው ወንድሜ/ የቆምሽው እህቴ" 
  • ”ዐሳብክን እንድትለውጥ ተስፋ የማደርገው ወንድሜ/እንድትለውጭ ተስፋ የማደርግሽ እህቴ” 
  • “የዐማራን ሕዝብና ዎገኖቹን ሕልውናና ነጻነት  እየጎዳህ ያለኸው ወንድሜ/ እየጎዳሽ ያለሽው እህቴ”
  • "በጨዋ አንደበት ብትናገር የማደንቅህ ወንድሜ/የማደንቅሽ እህቴ 
  • "የዐማራን ሕልውና ከሚጻረር ጋር የምትሠራ ወንድሜ/የምትሠሪ እህቴ"
  • "ዐማራን የሚጎዳ ዐሳብ የያዝከው ወንድሜ/የያዝሸው እህቴ 
  • "ዐማራን የሚጎዳ ሥራ እየሠራህ ያለኸው ወንድሜ/ ያለሽው እህቴ ወዘተርፈ የመሳሰለውን ለማለት ነው

    በእርግጥ "ባንዳ"ን/"ሆዳም"ን በኃይለ ቃል (በቁጣ) ለመናገር መጠቀም “ፍላጎትንና ግብን ለማስተላለፍ ዐይነተኛ ዘዴ የሚሆንበት ጊዜ እንዳለ አልስተውም። የኃይለኝነት ስሜትም ሳይሰጥ አይቀርም።የሁል ጊዜ ልማድ ማድረግ ግን በድምር ውጤቱ ለዐማራ ለበረከት የሚሆን አይመስለኝም። 

አሁን ባለበት ደረጃ ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ የመጋደሉ ጉዳይ ቀልድ እንዳልሆነ ለማንም ግልጽ ነው።ሕልውናንና ነጻነትን የማረጋገጡ ተጋድሎ የምር፣ የመረረና  አጣዳፊም ነው። በብዙ መቶ ሺህ ወይም ሚሊዮን ወገኖቻችን ነፍሳቸውን አስይዘው እየታገሉበት ያለ ሥራ ነው። ሲቪሉ የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹም በብዙ ጉስቁልናና ሥጋት ውስጥ ነው።እየሞቱ ያሉት ነጻነትን በማፈን ዐላማ ቢሆንም፤  የመከላከያና የሚሊሽያ አባላትም ዎገኖቻችን መሆናቸውና ጦርነቱ እንዲያጥርላቸው ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ከማንም የተደበቀ አይመስለኝም። ስለሆነም በገሀድም ሆነ በስውር ለተጋድሎው የለየለት እንቅፋት የሚሆንን ዎገን ለማስታመም የሚበቃ ጊዜ እንደሌለ የማይታየኝ አይደለሁም። እንዲህ ዐይነቱን እንቅፋት፣ ተሰሚነት እንዳይኖረው ማድረጉ ወይም ማግለሉ ቀን የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑ ይገባኛል።

በስተቀረ ግን የግራውንም የቀኙንም ሁሉ ባንዳ /ሆዳም ማለት የሰውን የመለወጥ ዕድል፣ የመሥራት ፍላጎት እንዲሁ አስተዋጽኦውን የሚያቀጭጭ እንጂ የሚያበረታታ አይመስለኝም።

በተያያዘ፦ ለረዥም ጊዜ (ቢያንስ ላለፋት አምስት ዐመታት) ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ሕልውናና ነጻነት ሳያወላውሉ በጽናት የታገሉን በአመራር ከፊት እንዲቆዩ ወይም እንዲመጡ መርዳት ለእኔ ለፖለቲካ መሃይሙ ለጥንቃቄ የሚረዳ ሆኖ ይሰማኛል።

ገባ ወጣ ያሉትንና የሚሉትን  ወይም ዐማራን ለመምራት ዕድሉን አግኝተው ከጉዳት ያልታደጉትን ፊት ለፊት በአመራርነት  አለማምጣት ብልህነት እንደሆነ ይታየኛል። እነርሱም ቢሆኑ እውነት ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ የሚቆረቆሩ ከሆነ ለተጋድሎው ማዋጣታቸውን እየገፉበት ለአመራር ሥፍራው ከሚያስተማምኑት ጋር መጋፋቱን ቢተውት እላለሁ።አዳዲስ ወጣት መሪዎችንም ወደፊት ማምጣት የሚበጅ ሆኖ ይሰማኛል። ይገባኛል፣ ይህ ዐሳብ ገራ ገር እንዳውም የቂላ ቂል ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጂ አንድ ዐሳብ ነው። 

  ለመደምደም፦የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ታማኝነቱ ከተጋድሎው ግብ እንጂ ከመሪው/መሪዋ አለመሆኑን ልብ ማለቱም ይበጃል።ማንም መሪ የዐማራን ሕዝብና ዎገኖቹን ሕልውናና ነጻነት በስውርም በግልጽም ከማገልገል ዞር ቢል ወይም ቢጠለፍ የተቆረበው ከተጋድሎው ግብ እንጂ  ከእርሱ/ ከእርሷ  ጋር አለመሆኑን  መረዳት ለመሪውም ለተመሪውም በረከት ይሆናል።  

ስለ አነበባችሁልኝ አመሰግናለሁ።

ደግሞ ባንዳ /ሆዳም በሉኝ አሉ!

Comments

Popular posts from this blog

Comparative Theology የነገረ መለኮት ንጽጽር (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት)/ በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሲኖዳ ሳልሳዊ

 የነገረ መለኮት ንጽጽር  (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት): የወደደ  ሁሉ በነጻ እንዲጠቀምበት ተፖስቷል። ይሁን እንጂ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ስለሆነ በየትኛውም መልኩ ለንግድ እንዲውል አልተፈቀድም። ልዩ ልዩ መግቢያ የሚለውን መጀመሪያ ካነበቡ በኋላ የተቀረውን በተመረጠው ቅደም ተከተል ማንበብ ይቻላል። ልዩ ልዩ መግቢያ   ጥምቀት   ትውፊት (ወግና ልማድ)   መካከለኝነት   ጾም የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ   ሥርዐት ንስሐ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ (1)  ድንግል ማርያምን ስለማክበር (2) ለጥያቄዎች መልስ (ሀ) ድንግሊትን ‘የወይን ግንድ (ተክል)’ና የ ‘ሕይወት በር’ የሚል ማዕረግ  ለምን እንሰጣታለን? (ለ) ወደ ድንግል ማርያም መጸለይ ትክክል ነው ወይ? (3) የድንግል ማርያም ድንግልና ዘላለማዊነት (4) ለተቃራኒ አስተያየቶች መልስ (ሀ) “የመጀመሪያ ልጇን” የሚለው ሐረግ (ለ) “ሚስትህ” የሚለው ሐረግ (ሐ) “አብረው ከመሆናቸው በፊት ጸንሳ ተገኘች” (መ) “የመጀመሪያ ልጇን እስክትወልድ አላወቃትም” (ሠ)  “ወንድሞቹ” የሚለው ሐረግ   የቅድስት ድንግል ማርያም  ክብሯ (1) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ድንግል እመቤታችንን አያከብሩም፤ ደግሞም እንድታማልድላቸውም (እንድትማልድላቸውም)  አይጠይቋትም።ከእነርሱ ወገኖች አንዳንዶቹ እንዲያውም ጫጩቱ ከተፈለፈለ በኋላ ዋጋ ከሌለው የዶሮ እንቁላል ቅርፊት ጋር እስከሚያመሳስሏት ይደርሳሉ።ይህ የተጋነነ ማቃለል የመጣው ምናልባት ሮሜዋውያን ካቶሊኮች የተጋነነ ማክበር ስለሚያከብሯት ለዛ ተቃርኖ ከማሳየት አዝማሚያ ሊሆን ይችላል። ስለዚህም ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን አንዱንም የእርሷን በዓል አያከብሩም።  (2) አንዳንዶቹ የፕሮቴስታንት ወገኖች ድንግል ማርያምን “እህታችን” ይሏታል። (3) በተጨማሪ አንዳንዶቹ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጌታ ኢየሱስን በድንግልና ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር ጋብቻዋን ፈጽማለች፤ የ‘ኢየሱስ ወንድሞች’  ወይም የ’ጌታ ወንድሞች’ ተብለው የተጠሩ ልጆችን ወልዳለች ይላሉ።  (4) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ቤተክርስቲያናችን ለድንግል እመቤታችን የሰጠቻቸውን አንዳንድ የማዕረግ ስሞችም ይቃወማሉ።  (5) ድንግልን ያለማክበራቸው አንዱ...

ስለ "አስታዋሽ ጾምና በዐሉ" ጥያቄና መልስ

 ስለ "አስታዋሽ ጾምና በዐሉ" ጥያቄና መልስ  ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ፦ ሕልውናችንን-ነጻነትችንን የማረጋገጥና የማስቀጠል አንድነታችንን የመጠበቅና የማጠንከር  በእሴቶቻችን የመደሰት፣ እነርሱን የመንከባከብና የማስተዋወቅ  በረከታችንን የማብዛትና የማካፈል  ኃላፊነቶቻችንን በማኅበር ፣ በማስተዋልና በትጋት እንድንወጣ “ጾሙና በዐሉ" አስታዋሽ ባሕላዊ ምልክታችን ይሁንልን   ጥያቄ 1 ፡ አድማጭ ተመልካቾቻችን እንኳን ደህና መጣችሁ።የከበረ ሰላምታችን ይድረሳችሁ። ዛሬ የምንወያየው ከአቶ ባንቱ ገብረማርያም ጋር ይሆናል። አቶ ባንቱ በሙያው ፋርማሲት ነው። እንደነገረኝ በእምነቱ ደግሞ ባፕቲስት ነው።ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ባሕላዊ ምልክት የሚሆን “ጾምና በዐልን” በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል። የምንወያየውም ስለዚሁ "ጾሙና በዐሉ" ምልክትነት ይሆናል።  አቶ ባንቱ ለመወያየት  ወደ እኛ በመምጣትህ አመሰግንሃለሁ። እንኳን ደህና መጣህ። አንተ እያልኩ ልቀጥል ወይስ አንቱ? መልስ 1፡ ዎገኔ፡   እንኳን ደህና ቆየኸኝ። ለአድማጭ ተመልካቾቻችሁም ሰላምታዬ ይድረስልኝ። አንተ በለኝ። የሚያውቀኝ ሁሉ አንተ ነው የሚለኝ።  ጥያቄ 2 ፡ እሺ  አንተ እያልኩ እቀጥላለሁ። አቶ ባንቱ፣ ምናልባትም ብዙ ሰው ስለማያውቅህ  እስቲ ስለራስህ በአጭሩ ንገረን። ወዲያውም መክፈቻ ይሆነናል መልስ 2 ዎገኔ ፦ አስቀድሜ ይኸን ዕድል ስለሰጠኸኝ ላመሰግንህ እወዳለሁ። አድማጭ ተመልካቾችህንም ጊዜ ወስደው  ውይይቱን  ስለሚከታተሉ ላመሰግናቸው እወዳለሁ።አዎን፣ ባንቱ ገብረማርያም እባላለሁ።እንደነገሩኝ የተወለድኩት ሽርካ በዛሬ አጠራሩ በአርሲ ዞን ነው።ነፍስ ያወቅሁትና ትምህርት ...