Skip to main content

ንቄው ነበር

 ንቄው ነበር!

የገጠመኝን ታሪክ ላውጋችሁ። ከ30 ዓመት በፊት የሆነ  ነው። የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ሦስት ወጣት ፍልስጤማውያን ነበሩ። ከአንደኛው ጋር እንዳውም አንድ ሪደር  (ፕሮፌሰር) ነበረን።ታዲያ ወንድማቸው ስለሆነው የአይሁድ ሕዝብ ባወራን ጊዜ 

<<ልታስተናግደው መኝታ ቤት የሰጠኸው ሰው ቤትህን ሲቀማህ ዝም ብለህ ታየዋለህ እንዴ? እኛም አይሁዶችን የምናያቸው እንደዛ ነው። ምኞታችን ሁሉ ትምህርታችንን  ጨርሰን እነርሱን መውጋት ነው >> 

ብለውኝ ነበር።

 የተላኩ(ህ)በትን ትምህርት እንደምንም ጨርሼ ትምህርት ቤቱን ከተለየሁ ወዲህ ግንኙነት ስለሌን ያድርጉት ፥ አያድርጉት አላውቅም። ሁላችንም “የሰው አገር ሰው” መሆናችን አቆራኝቶን ነበርና በጊዜው ግን እንቀራረብ ነበር።ታዲያ ከዕለታት አንዱን ቀን፥  የጾም ፍቺያቸው ጊዜ ይመስለኛል (አሁን ተዘንግቶኛል) ልጎበኛቸው እቤታቸው ሄድኩ። አንድ “የታላቁን የዐረብ ኢምፓየር”  ካርታ እስቲከር  በቤታቸው ግድግዳና በብዙ ሥፍራ ተለጥፎ አየሁ።ተገረምኩም። ኢትዮጵያ ጭምር “የአፍሪካ ቀንድ” አገሮች በዚያ ካርታ ተጨምረው ነበርና። 

<<ይህ ደግሞ ምንድነው? ኢትዮጵያ እዚህ ውስጥ እንዴት ተጨመረች?>>

 ብዬ ጠየቅኋቸው።ተደናገጡ። ሊያስረዱኝም ሞከሩ።

 <<የነቢያችን ተከታዮች ዐበሻ አገር በተጠለሉ ጊዜ ነጋሻቸው ሙስሊም ሆኖ ነበር>>

 አሉኝ። ሆኖም ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያን በዐረብ አገር ለማካተት  ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አልታየኝም። አፈጣጠራቸውም ታሪካችውም ለየቅል ነውና።ይሁን እንጅ አልተንጨረጨርኩም።

 <<ምንም አይደለም፥ ይህን ኢምፓየር  ንጉሥ  ሆና ኢትዮጵያ እስከገዛች ድረስ አያጣላንም>> 

ብዬ ቀልጄ አለፍኩ። የዚያ አካባቢ ልጆች ምን እየተነገራቸው እንደሚያድጉም በእግር መንገዴን ገመትሁ።የሄድኩበትን ትምህርት እስከምጨርስ ድረስ ወዳጅነታችን አልተቋረጠም ነበር። ይህ ገጠመኝ ሰሞኑን ትዝ አለኝ። ንቄ ትቼው የነበረውን ይህን አስታውሼ:-

<<የመጀመርያው የታላቁ ዐረብ ኢምፓየር ንጉሥ ለማድረግ አስቀድሞ  ዐረባዊ መልክ ለማልበስ ይሆን እንዴ ከኢምሬት በሚገኝ ሁለንተናዊ ድጋፍ ኢትዮጵያ እንዲህ  የምትመሰቃቀለውና ከመሠረቷ የምትናደው?>> ብዬ መጠርጠር ጀመርሁ።



Comments

Popular posts from this blog

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ (1)  ድንግል ማርያምን ስለማክበር (2) ለጥያቄዎች መልስ (ሀ) ድንግሊትን ‘የወይን ግንድ (ተክል)’ና የ ‘ሕይወት በር’ የሚል ማዕረግ  ለምን እንሰጣታለን? (ለ) ወደ ድንግል ማርያም መጸለይ ትክክል ነው ወይ? (3) የድንግል ማርያም ድንግልና ዘላለማዊነት (4) ለተቃራኒ አስተያየቶች መልስ (ሀ) “የመጀመሪያ ልጇን” የሚለው ሐረግ (ለ) “ሚስትህ” የሚለው ሐረግ (ሐ) “አብረው ከመሆናቸው በፊት ጸንሳ ተገኘች” (መ) “የመጀመሪያ ልጇን እስክትወልድ አላወቃትም” (ሠ)  “ወንድሞቹ” የሚለው ሐረግ   የቅድስት ድንግል ማርያም  ክብሯ (1) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ድንግል እመቤታችንን አያከብሩም፤ ደግሞም እንድታማልድላቸውም (እንድትማልድላቸውም)  አይጠይቋትም።ከእነርሱ ወገኖች አንዳንዶቹ እንዲያውም ጫጩቱ ከተፈለፈለ በኋላ ዋጋ ከሌለው የዶሮ እንቁላል ቅርፊት ጋር እስከሚያመሳስሏት ይደርሳሉ።ይህ የተጋነነ ማቃለል የመጣው ምናልባት ሮሜዋውያን ካቶሊኮች የተጋነነ ማክበር ስለሚያከብሯት ለዛ ተቃርኖ ከማሳየት አዝማሚያ ሊሆን ይችላል። ስለዚህም ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን አንዱንም የእርሷን በዓል አያከብሩም።  (2) አንዳንዶቹ የፕሮቴስታንት ወገኖች ድንግል ማርያምን “እህታችን” ይሏታል። (3) በተጨማሪ አንዳንዶቹ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጌታ ኢየሱስን በድንግልና ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር ጋብቻዋን ፈጽማለች፤ የ‘ኢየሱስ ወንድሞች’  ወይም የ’ጌታ ወንድሞች’ ተብለው የተጠሩ ልጆችን ወልዳለች ይላሉ።  (4) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ቤተክርስቲያናችን ለድንግል እመቤታችን የሰጠቻቸውን አንዳንድ የማዕረግ ስሞችም ይቃወማሉ።  (5) ድንግልን ያለማክበራቸው አንዱ...

Comparative Theology የነገረ መለኮት ንጽጽር (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት)/ በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሲኖዳ ሳልሳዊ

 የነገረ መለኮት ንጽጽር  (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት): የወደደ  ሁሉ በነጻ እንዲጠቀምበት ተፖስቷል። ይሁን እንጂ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ስለሆነ በየትኛውም መልኩ ለንግድ እንዲውል አልተፈቀድም። ልዩ ልዩ መግቢያ የሚለውን መጀመሪያ ካነበቡ በኋላ የተቀረውን በተመረጠው ቅደም ተከተል ማንበብ ይቻላል። ልዩ ልዩ መግቢያ   ጥምቀት   ትውፊት (ወግና ልማድ)   መካከለኝነት   ጾም የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ   ሥርዐት ንስሐ

ጥምቀት

  ጥምቀት       (1) የጥምቀት ፍቱንነቱ (2) ማጥመቅ የካህን ተግባር ነው (3) የጥምቀት አስፈላጊነቱ (4) ጥምቀት በመንከር (በመጥለቅ) (5) የልጆች (የሕጻናት) ጥምቀትሳቦች (6) ተቃውሞዎች   ጥምቀት   በእኛ በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንቶች መኻል ጥምቀትን በተመለከተ ያሉት ልዩነቶች የጥምቀትን ትምህርት በአምስት ጉልህ   ፍሬ ነገሮች ሥር አጠቃሎ መነጋገር ይቻላል። (1)     የጥምቀት   አስፈላጊነቱ   ምንድነው? ፍቱንነቶቹስ (ጠቀሜታዎቹስ) ምንድናቸው? ኦርቶዶክስ ጥምቀት ‘ድኅነት’ን፣ ‘መንጻት’ን፣ ‘መጽደቅ’ን፣ የ‘ሕይወት መታደስ’ን እና በ’ክርስቶስ አካል አባል’ መሆን’ን መቀበያ መንገድ ነው ብላ ታምናለች። የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች እንደሚሉት እነዚህን   መቀበያው “እምነት” ብቻ ነው። በ እምነት ብቻ መሆኑ ትክክል ከሆነ ታዲያ የጥምቀት አስፈላጊነቱ ምኑ ላይ ነው? የክርስትና ምልክት ብቻ መሆኑ ነውን? ወይስ “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው” (ማቴ 28:19-20) የሚለውን የጌታን ትዕዛዝ መታዘዝ ብቻ መሆኑ ነው? (2 ) ማነው ማጥመቅ ያለበት? በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጥምቀት የሚከናወነው በካህን ብቻ ነው። ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ግን የሰውን ክህነት ጨርሶ አይቀበሉም። ስለሆነም በእነርሱ ቤተ ክርስቲያን የሚያጠምቀው ካህን ወይም ቄስ ያልሆነ አገልጋይ ነው።   ይህ አገልጋይ የቤተክርስቲያኒቷ ሽማግሌ ወይም ሴት ሽማግሌ (የሴቶችን ሽምግልና ...