Skip to main content

Posts

Showing posts from September, 2025

Venerating Blessed Mary: ብፅዕት ማርያምን የማክበር ጉዳይ ማወኩ!

  ብፅዕት ማርያምን  የማክበር ጉዳይ ማወኩ? በባንቱ ገብረማርያም አድማጭ ተመልካቾቼ፡ እንደምን አላችሁ ? ክብሩ ይስፋ የመድኃኒዓለም ! እኔ ደህና ነኝ ሰሞኑን የማርያም ሥዕል መቀደዱን ከማህበራዊ መገናኛ ተመለከትኩ። ስለዚያ ያለኝን አስተየየት እንደሚከተለው አቀርባለሁ። እንድትከታተሉት በታላቅ ትህትና እጋብዛችኋለሁ።        በመጀመሪያ ስለ ማርያም ሥዕል ያለኝን ትውስታ ልንገራችሁ። በጎባ / ባሌ የአዝማች ደግልሃን ት / ቤት   ተማሪ ነበርኩ ( ስሙ ተቀይሯል ) ። ይህ ታሪክ የሆነ ጊዜ የስንተኛ ክፍል ተማሪ እንደነበርኩ አሁን ተዘንግቶኛል። የዘጠነኛ   ወይም የአሥረኛ   ክፍል   ተማሪየነበርኩ ይመስለኛል። በዚያን ዐመት በትምህርት ቤቱ የተማሪ ክበቦች ተቋቁመው ነበር።ታዲያ እኔም ከተቋቋሙት አንዱ ከነበረው ከመጽሐፍ ቅዱስ ክበብ   ገባሁኝ። የክበቡ መሪ ከቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ዩኒቨርስቲ ( ስሙ ተቀይሯል ) በብሔራዊ አገልግሎት የመጣ የኬሚስትሪ   አስተማሪ ነበር። አንዱን ቀን መጽሐፍ ቅዱስን ሊያስተምረን አባላቱን   ሚካኤል ጋራ ላይ ይዞን ወጣ ( አካባቢውን ለማታውቁት ሚካኤል ጋራ ከትምህርት ቤቱ ጀርባ የተቆለለ ጋራ ነው ) ። እዚያ ስብሰባ ላይ ነበር የማርያምን ሥዕል   ያደለን።የሥዕሉ   ትልቅነቱ   የኪስ ቦርሳ ውስጥ ለማስገባት የሚያስቸግር ያህል ነበር።እጅግም ትልቅ አልነበረም ለማለት ነው። ት / ቤት   ለዕረፍት በተዘጋበት ጊዜ   ...

የአማሮች አባት ኑዛዜ

 ይህን ለልጆቻችሁ ማካፈል ትችላላችሁ? የአማሮች   አባት ኑዛዜ                ዘመኑ ቆይቷል። የሚሆነው ነገር አይታወቅም በማለት ትልቁን - ዋርካ አባታቸውን - የአማሮቹን አባት - ተቀጣጥረው ሊጎበኙት   ሄደው ነበር።ታዲያ እነዚያ ሊጠይቁት የሄዱት ተወላጆቹ ዋርካውን ቀድሞ ያዩት እንደነበር ሆኖ አላገኙትም። ለወትሮ ደጅ ፣ ደጅ ሲል ፣ሲንጎራደድ ነበር የሚያገኙት።ያን እለት ግን አልጋ ላይ ውሏል። ሲያያቸው ደስ አለው።ሰላምታ ተለዋወጡ። ተነቃቅቶም   ቀና ለማለት ሞከረ። በወጉ ተቀምጦ ሊያጫውታቸው ፈለገና   ወገብ ከየት ይምጣ ? ደጋግፈው   አስቀመጡት። ከዚያም ጉሮሮውን አጥርቶ ያናገራቸው ጀመር።እነርሱም ጸጥ ብለው ሊያዳምጡት ገቡ። “ ዕድሜ ጠገብኩ አይባልም እንጂ ብዙ ዘመን ኖሬአለሁ።ይህን ያህል ዘመን እኖራለሁ ብዬ አላሰብኩም ነበር።ብዙ ትውልድ አሳለፍኩኝ። እንደ እኔ በዕድሜ የጠገቡ ያሉ አይመስለኝም ። አሁን ግን ያ ክፉ ሰው - እርጅና መጥቶብኛል። አልጋ ላይ ከዋልኩ ሰነባበትኩ። ሕልፈተ ሞቴም   የደረሰ ይመስለኛል።የአብራኬ ክፋዮች፣ ልጆቼ፣ ዝርያዎቼ አስታውሳችሁኝ ልትጠይቁኝ ስለመጣችሁ ተባረኩ።ምሩቅ ሁኑ። ዳግመኛ ላታዩኝ ትችላላችሁና ዛሬ ትዝታዬንም ትውስታዬንም ላውጋችሁ። ኑዛዜ ብትሉትም ይሆናል አደራዬንም አሸክማችኋለሁ። ” አለ " እሺ እናዳምጥሃለን ! አባታችን። ንገረን አለ - ከመኻላ...