Skip to main content

ፋኖ ፡ በኢትዮጵያ የሃያ አንደኛው ምዕተ ዐመት ልዩ ክስተት

 


ፋኖ ፡ በኢትዮጵያ የሃያ አንደኛው ምዕተ ዐመት ልዩ ክስተት 

የኢትዮጵያን ሁኔታ ከዜና አቅራቢዎች  እንደሚከታተል ሰው በዚችው ጥቂት ዕድሜዬ በርካታ ፓለቲከኞች ተነስተው አይቼአለሁ። አስተዋጽኦዋቸውን በጓዳዬ ያደነቅኋቸው ብዙ ናቸው። ከእነዚህ መኻል ባስቀመጥኳቸው ሥፍራ ያላገኘኋቸው  አሉ።ድርጅቶቻቸውም  እንደዚያው የሆኑባቸው። ያዘንኩላቸውም ያዘንኩባቸው ይኖራሉ። ችግራቸውንና  ፈተናቸውን እነርሱ ያውቃሉ። እኔ በሩቅ ሆኜ የምከታተል ስለሆንኩ እሳቱ ምን ያህል እንደፈጃቸው ልረዳላቸው አልታደልኩም። 

አሁን ላይ ከእነዚህ መኻል  የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹን ለማዳን ኃላፊነቱን በሚገባ እየተወጣ ያለውን ፋኖ፣ ለመለወጥ ወይም ለማደናቀፍ ወይም ጠልፎ ለመጣል የሚሠሩትን  ግን  ተቀይሜአቸዋለሁ። የዐማራ ስቃይን ለዘለቄታው  ማስወገድ እስከቻለ ድረስ ማንስ ፋኖን ቢመራው ምን ቸግሯቸዋል?  ቀጥታ በተጋድሎው ሥፍራ  ላይ ያሉት የፋኖ መሪዎች ያጎደሉት ምን ኖሮ ነው? እንደ እኔ ዐሳብ ይህን ትተው በመተባበሩ ላይ ቢያተኩሩ ለሁላችንም ድንቅ ይሆናል እላለሁ። ደግሞ ይኸንን ያጡታል ብዬ አላስብም። መተባበሩን ይመርጣሉም ብዬ አምናለሁ።

ለማንኛውም በስፋት ሲዘገብ እንዳገኘሁት ፋኖዎች 

  • unchecked

    ሞትን ሳይፈሩ፥ ደፍረው ፥ በነፍሳቸው ቆርጠው

  • unchecked

    ጉልበታቸውን በደሊላዎች ሳያደክሙ 

  • unchecked

    ገንዘብንም ሎሌያቸው እንጂ ገዥያቸው ሳያደርጉ 

  • unchecked

    በቅርብም በሩቅም ባሉ ወንድሞቻቸው የሸፍጥና  የኅይል ሥራ ሳይርዱ

  • unchecked

    የዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ እንዳይጐዳ እየተጠነቀቁለትና እርሱም እየደገፋቸው

  • unchecked

    አብዛኞቹ መሪዎቹ ለዐማራ ሕዝብ በረከት ሲሉ  የግል ኢጎአቸውን በመዋጥ  ወደ መተባበርና ማበር እየተመነደጉ 

  • unchecked

    የፊት ለፊት አጥፊዎችንና አጥቂዎችን  ሁሉ ተቋቁመው ተገዳዳሪ ኅይል ሆነው ወጥተዋል። ይህ በኢትዮጵያ የ21ኛው ምዕተ ዐመት ልዩ ክስተት ነው እላለሁ። ፋኖዎች እዚህ ላይ  በመድረሳቸው እጄን በአፌ ላይ አስጭነውኛል። እንዳውም መለኮታዊ ጣልቃ  ገብነት ሳያግዛቸው አልቀርም እላለሁ።

(ነፍሳቸውን ይማርና) ፕሮፌሰር መስፍን  ያኔ ጎንደር  -ጎጃም -ወሎ -ሸዋ  እየተባለ ይጠራ ስለነበረው አካባቢ  በአንድ የጥናት ጉባኤ ላይ የተናገሩትን አስታውሳለሁ። “አገሪቷ ያሏት ምርጥ ተዋጊዎች የሚገኙበት አካባቢ ነው” ሲሉ ሰምቼአቸው ነበር። ታዲያ ያንን  ሰምቼ “ዐማራው ይኽን ያህል መከራ ሲያይ፣ በሥጋት ታጥሮ እየተዋከበ እያዩት ፥የተባሉት ተዋጊዎች የታሉ”? እያልኩ እኖሮ ነበር።  የዐርበኛ ጎቤ ብቅ ማለት ለመጀመሪያ ጊዜ  ለዚህ ጥያቄዬ መልስ ሆነኝ። “ጀግና ሸክላ  ነው”  ማለት እውነት ነው መሰለኝ  ብዙም ሳይቆዩ ተሰውተዋል (በወቅቱ  የቅርብ ዘመዴ የሞተ ያህል ሃዘን ተሰምቶኛል)። ‘በአምላኩ ተሰማ’  የሚል ቅጽል ስም ለራሴ እንዳወጣ ምክንያት ሆነውኝ አልፈዋል። ለካንስ እነሻለቃ መሳፍንትም ኖረዋል (የለውጥ በሩ ተበርግዶ ከተጋድሎው ሥፍራቸው ብቅ ያሉ ጊዜ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ በቴሌቪዥን መስኮት ያየኋቸውና  ያወቅኋቸው)። እነዚህ  ፈር የቀደዱለት የመሰለኝ አዲሱ ፋኖነት ዛሬ  እልፍ አእላፋትን ማርኳል።የአብርሃም አምላክና አምላካችን ለመጨረሻው ድል ያብቃው። 

አዎን በልጅነቴ እንዳየሁት ኢትዮጵያውያን በፍቅር መኖር እንድንችል በሩን ለመክፈት ያብቃው።

ቸር እንሰንብት!

ዎገናችሁ ነኝ




Comments

Popular posts from this blog

Comparative Theology የነገረ መለኮት ንጽጽር (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት)/ በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሲኖዳ ሳልሳዊ

 የነገረ መለኮት ንጽጽር  (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት): የወደደ  ሁሉ በነጻ እንዲጠቀምበት ተፖስቷል። ይሁን እንጂ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ስለሆነ በየትኛውም መልኩ ለንግድ እንዲውል አልተፈቀድም። ልዩ ልዩ መግቢያ የሚለውን መጀመሪያ ካነበቡ በኋላ የተቀረውን በተመረጠው ቅደም ተከተል ማንበብ ይቻላል። ልዩ ልዩ መግቢያ   ጥምቀት   ትውፊት (ወግና ልማድ)   መካከለኝነት   ጾም የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ   ሥርዐት ንስሐ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ (1)  ድንግል ማርያምን ስለማክበር (2) ለጥያቄዎች መልስ (ሀ) ድንግሊትን ‘የወይን ግንድ (ተክል)’ና የ ‘ሕይወት በር’ የሚል ማዕረግ  ለምን እንሰጣታለን? (ለ) ወደ ድንግል ማርያም መጸለይ ትክክል ነው ወይ? (3) የድንግል ማርያም ድንግልና ዘላለማዊነት (4) ለተቃራኒ አስተያየቶች መልስ (ሀ) “የመጀመሪያ ልጇን” የሚለው ሐረግ (ለ) “ሚስትህ” የሚለው ሐረግ (ሐ) “አብረው ከመሆናቸው በፊት ጸንሳ ተገኘች” (መ) “የመጀመሪያ ልጇን እስክትወልድ አላወቃትም” (ሠ)  “ወንድሞቹ” የሚለው ሐረግ   የቅድስት ድንግል ማርያም  ክብሯ (1) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ድንግል እመቤታችንን አያከብሩም፤ ደግሞም እንድታማልድላቸውም (እንድትማልድላቸውም)  አይጠይቋትም።ከእነርሱ ወገኖች አንዳንዶቹ እንዲያውም ጫጩቱ ከተፈለፈለ በኋላ ዋጋ ከሌለው የዶሮ እንቁላል ቅርፊት ጋር እስከሚያመሳስሏት ይደርሳሉ።ይህ የተጋነነ ማቃለል የመጣው ምናልባት ሮሜዋውያን ካቶሊኮች የተጋነነ ማክበር ስለሚያከብሯት ለዛ ተቃርኖ ከማሳየት አዝማሚያ ሊሆን ይችላል። ስለዚህም ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን አንዱንም የእርሷን በዓል አያከብሩም።  (2) አንዳንዶቹ የፕሮቴስታንት ወገኖች ድንግል ማርያምን “እህታችን” ይሏታል። (3) በተጨማሪ አንዳንዶቹ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጌታ ኢየሱስን በድንግልና ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር ጋብቻዋን ፈጽማለች፤ የ‘ኢየሱስ ወንድሞች’  ወይም የ’ጌታ ወንድሞች’ ተብለው የተጠሩ ልጆችን ወልዳለች ይላሉ።  (4) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ቤተክርስቲያናችን ለድንግል እመቤታችን የሰጠቻቸውን አንዳንድ የማዕረግ ስሞችም ይቃወማሉ።  (5) ድንግልን ያለማክበራቸው አንዱ...

ከቄስ ( ዶ/ር ) ቶሎሳ ይልቅ

 አድማጭ ተመልካቾቼ አንደምን ከረማችሁ? የአብርሃም አምላክና አምላካችን የተመሰገነ ይሁንና እኔ ደህና ነኝ።"ከቄስ (ዶ/ር ) ቶሎሳ ይልቅ" በሚል ርዕስ ያዘጋጀሁትን  የሚከተለውን መልዕክቴን እንድትከታተሉልኝ በታላቅ አክብሮት እጠይቃችኋለሁ። ባንቱ ገብረማርያም ነኝ ከቄስ (ዶ/ር) ቶሎሳ ይልቅ           ቄስ (ፓስተር) ዶ/ር ቶሎሳ  ጉዲና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን በአትላንታ/ጆርጂያ ፓስተር መሆናቸው በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅ ይመስለኛል። በበኩሌ የማከብራቸውም ሰው ናቸው። በወንጌላውያን መኻል ለበርካታ ዐመታት ለኢትዮጵያ ሰላምና አንድነት የተናገሩ፣ ያሳሰቡና የጸለዩ መሆናቸውን ሰምቼአለሁ።በነገዳቸው የተደራጁትን የወንዛቸው ልጆችን ወቀሳ ተቋቁመው ለመላው ኢትዮጵያዊ ሲጮኹ የኖሩ ናቸው።           ስለ እሬቻ የሰጡት ትምህርት እስከዛሬ እንደሞዴል የማየው ነው። እሬቻን እንዳይከተሉና እንዳያስፋፉ የአሁኖቹን የመንግሥት ዐላፊዎች የመከሩበትንም ጊዜ አስታውሳለሁ።           የወንጌላውያን ሽማግሌ ብቻ ሳይሆኑ በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ የአገር ሽማግሌ አድርጌ አያቸዋለሁ። ይህን መደላድል የማስቀምጠው ስለእርሳቸው ያለኝን አስተያየት ለማስታወቅና ይኸው ሐሳቤ የጸና መሆኑን ለማስጮህ ነው።አስተያየቴን አልጠየቁኝም፣ የሚጨምርላቸውም ሆነ የሚቀንስባቸው ነገር እንደማይኖርም ጠንቅቄ አውቃለሁ። መደላድሉን አስቀድሜ  ማስቀመጤ ወንድሞችንና እህቶችን “አይዟችሁ አትደንግጡ” ለማለት ያህል ነው። ...