Skip to main content

ፓስተር ታምራት ኃይሌ፡ አመሰግናለሁ!

 


እድማጭ ተመልካቾቼ እንደምን አላችሁ? ቸርነቱ የማያልቅበት አምላክ ይመስገንና እኔ ደህና ነኝ።ዛሬ ፓስተር ታምራት ኃይሌ በቅርቡ ባሰማውልመናላይ ያለኝን አስተያየት አጋራለሁ። እንድትከታተሉልኝ በታላቅ ትህትና እጋብዛችኋለሁ።

ባንቱ ገብረማርያም ነኝ

ርእሱፓስተር ታምራት ኃይሌ፡ አመሰግናለሁ! (ከታምራት ላይኔ ጋር አይምታታ)

  መነሻዬ ሰሞኑን ፓስተር በዩትዩብ ያቀረበው መልዕክት ነው። ማዳመጥ ለሚፈልግ ሊንኩን እያይዤዋለሁ።

ፓስተር ታምራት ለመንግሥት፣ መንግሥትን ለሚዋጉና እንዲሁም በዲያስፖራ ላለነው በወግ በወጉ አደራጅቶ ልመና አቅርቧል። መጀመሪያ ልመናውን በራሴ አገላለጽ በአጭሩ አኖረውና ከዚያ ወደ አስተያየቴ እገባለሁ፡፡ 

ልመና ፩፡ ለመንግሥት የቀረበ

ብዙ ልጆች የወለደ አባት የሁሉን ልጆች ፍላጎት አስማምቶ ማርካት እንደሚቸግረው ሁሉ የሕዝቦች አባትና ጠበቃ የሆነው መንግሥትም የሁሉንም ሕዝቦች ፍላጎት መሙላት ሊያስቸግረው ይችላል። ዋናዎቹን በተመለከተ ግን ከእግዚአብሔርም ከሕዝብም የተሰጠው አደራ ስለሆነ ገሸሽ ሊያደርጋቸው አይገባም ይላል ፖስተር  ታምራት ኃይሌ ሲጀምር። በመቀጠልም ዋናዎቹን እደራ ይዘረዝራል፦

  1. አገርን ማልማትና የዜጎችን ሕይወት መቀየር 
  2. ዜጎች በአገራቸው በሰላም ሠርተው፣ ሐብት አፍርተውና ተጋብተው፣ ተዋልደው እንዲኖሩ የሰላምና የደኅንነት ዋስትና ማረጋገጥ 
  3. የአገርን ዳር ድንበር ከማናቸውም ወራሪ መጠበቅና አገርን በሉዐላዊነት ማቆየት 
  4. የሰላም ችግር ሲታይ ሳይውል ሳያድር ፈጥኖ ሰላምን መልሶ ማስፈን (ኢትዮጵያን ከዳር እሰከ ዳር የጥይት ድምጽ የማይሰማበት አገር ማድረግ) ናቸው።

ከዝርዝሩ በኋላ፦

    ከእግዚአብሔርም ከሕዝብም በተሰጠው በዚህ አደራ መሠረት የሕዝቦችን ጥያቄዎች አዳምጦ፣ የተፈለገውን መስዋእትነት ከፍሎም ቢሆን፣ ቢያስፈልግ ወደ ኋላ አጎንብሶአሁን በአማራ ክልል፣ እንዲሁምአነሱ-በዙዳር ሆኑ-መኻልሳይባል በሌሎችም ክልሎች ያለውን ጦርነት መንግሥት በአስቸኳይ እንዲቆም እንዲያደርግ ይለምናል። በልመናው ውስጥ የሕዝቦችን ሰላምና አንድነት መጠበቅን እንዲሁም የልማት አውታሮችንና የሕዝብ ንብረትን ከጥፋት መታደግ አስፈላጊነትን አስምሮባቸዋል። 

ልመና ፪፡ መንግሥትን ለሚዋጉት፡ 

 ተሞክሮችን ለማስረጃነት ጠቅሶ - "ዛሬ ማሸነፍ እንዳለ ነገ መሸነፍ ስላለ ኃይል ዘላቂ መፍትሔ ያመጣ መስሏችሁ አትታለሉ፣ መነጋገሩን ብቻ አማራጭ አድርጉ። ምን ቢቸግራችሁ የኃይል አማራጭን አትጠቀሙ። እርግፍ እድርጋችሁ ተውት" ብሎ ይመክራቸዋል።  

ልመና : ለዲያስፖራው፡  

ጦርነቱ የሚጎዳው የራሳችሁን ወገን መሆኑን ተረድታችሁ እባካችሁ መከረኛውን ሕዝብ እንዲዋጋ አትቀስቀሱት በማለት ይማጸናቸዋል

ልመናዎቹ እኔ እስከተረዳኋቸው ድረስ እነዚህ ናቸው። ያጎዳልኩት ካለ ይቅርታ እጠይቃለሁ። 

አሁን ወደ አስተያየቴ፡

ከልመናው መንፈስ እንደምረዳው የኢትዮጵያ ሕዝብ ህመምና ስቃይ ፓስተር ታምራትን ያሳሳበው እንደሆነ ይነበባል። የመቃተት፣ የጩኸት ድምጽ ነው የጮኸው። ሕዝቡ እርፍ ብሎ እንዲኖርለት ይፈልጋል። ምናልባት ዘግይቷል ይባል እንደሆን እንጂ ለሥጋ ወገኖቹ ለኢትዮጵያውያን የተሰማውን የሃዘኔታና የርኅራሄ  ስሜት  በብልሃት ገልጧል እላለሁ። ከሕሊና ወቀሳም፣ ከታዛቢ ክስም ተርፏል  

ለበርካታ ፓስተሮችም ለሥጋ ወገኖቻቸው ለኢትዮጵያውያን የተቆርቋሪነት ስሜታቸውን በይፋ እንዲገልጡ መንገዱን ጠርጎላቸዋል ማለትም እችላለሁ። ልመናው "ወንጌላውያን ካውንስሉንም" ዐይን ይገልጣል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። 

መንግሥትን ለሚወጉትና ለዲያስፓራው የተናገረውን ሐሳብ በተመለከተ ተመሳሳዩን ወይም ተቀራራቢውን ሐሳብ ከእኛ ሰፈር የተናገሩ ይገኛሉ ፓስተር ታምራት ግን በቅጡ አደራጅቶና አብራርቶ  አቅርቦታል። ከዚህ የተነሳ እነዚያ መንግሥትን የሚዋጉትናጦርነት ቀስቃሽየሚላቸው ዲያስፖራዎችም ልመናውን ለመረዳት ይከብዳቸው አይመስለኝም።

መንግሥትን በተመለከተ ኃላፊነቱን ማስታወሱና ሰበብ ሳያበዛ ይኸንኑ ኃላፊነት እንዲወጣ  መለመኑ ሕሊናን የሚያድስ ነው። ምክንያቱም መንግሥትን የሚያንቆለጳጵሰው እንጂ መሠረታዊ  ኃላፊነቱን  እንዲወጣ የሚያሳስበው ድምጽ በይፋ እጅግም ከማይሰማበት ከእኛ ሰፈር የወጣ ነውና

ምን አደከማችሁ፦ የትኞቹም ወገኖች ተግባራዊ እንዲያደርጉት የሚገደዱበትን መንገድ ባያውቅልንም (ያውቅ ከነበረም አልገለጠልንም) በበኩሌ ሐሳቡ እንደ ሐሳብ እፁብ ድንቅ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። በእርግጥ ሐሳቡን ሁሉም ላይገዛው፣ የለመናቸው ወገኖችም ላይሰሙት ይችላሉ የሚል ጥርጣሬ አለኝ እንደ ሐሳብ የወደድኩት መሆኔን ግን መሸሸግ አልተቻለኝም።

መደምደሚያ 

ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት ከሆነ አገሬ ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ትልቅ ምስቅልቅል ውስጥ ትገኛለችማመሰቃቀሉን ማን ጀመረው?” ለሚል ጥያቄ፦ዶሮ ናት የቀደመችው ወይስ እንቁላል ነው የቀደመው?” የሚለውን ለመመለስ የሚከብደ‍ውን ያህል የሚከብድ አይመስምለኝም ቢያንስ እየተዋጉት ካሉት ስለ"አንዳንዶቹ" በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል።

ወደ ጦርነት ከመግባታቸው በፊት ፖስተር በዘረዘረው አደራ መሠረት መንግሥት ሊመልስ ይገባቸው የነበሩ ጥያቄዎችን አቅርበው ስላልተመለሱላቸውና እንዳውም ጦርነት ስለተከፈተባቸው የመከላከል ጦርነት ውስጥ የገቡ ናቸው።  

ማስተዳደር ቀላል እንዳልሆነ እገነዘባለሁ፡፡ነገር ግን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር / አብይ አሕመድ እንደ ነገሩን ሥልጣኑን የያዙት ለብዙ ጊዜ ተዘጋጅተውበት ነው። ብዙ ወንድና ሴት አማካሪዎችም አሏቸው።የትኛውም የቀደመ የኢትዮጵያ መሪ ያላገኘውን የሕዝብ ድጋፍ አግኝተው ነበር። አገሪቷ ሀብት የምታገኝበት ዘዴም ምንጩም በእጃቸው ነው ያለው።  እልቆ  መሳፍርት የሌለው የፕሮፓጋንዳ መስመር አላቸው።ማስተዳደር ተስኖኛልም ሲሉ አልሰማኋቸውም። ስለዚህ አሁን በኢትዮጵያ የሚታየውን ምስቅልቅ ከመድረሱ በፊት ዘዴ ሊያበጁለት በቻሉ ነበር ለማለት ያስደፍረኛል።ሆኖም ሳያደርጉት ቢቀሩ ይሆናል  እነሆ እዚህ ምስቅልቅል ላይ ደርሰናል።

    ብቻ ያለፈው አልፏል።ምናልባት (እንዳው ምናልባት) አሁን የፓስተር ታምራት ኃይሌ ልመናን ሰምተው፣ ቢያስፈልግወደ ኋላ አጎንብሰው” (የፓስተር ቃልን ልዋስና) ስህተቶችን ለማረም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይነሳሉ ብዬ ተስፋ ላድርግ። ያን ጊዜ የሚዋጉትም ያቆማሉ። ዲያስፖራዎችም ጊዚያቸውንና ገንዘባቸውን ለጦርነት ከማዋጣት ይታቀባሉ። ሰበብም ሆነ ምክንያት አይቀርላቸውምና። በእርግጥ ልመናውን ሰምተው ፋኖዎቹም ሆኑ ሌሎች መንግሥትን የሚወጉ ኃይሎች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ጠመንጃቸውን ወደ ታች ለማዘቅዘቅ ሊመርጡ ይችላሉ። ጦርነት ቀስቃሽየተባልነው እኛም ዲያስፖራዎች እንዲሁ ምላሳችንን።ግና የማሸነፍ ዕድል አለኝ  የሚል ይህን ያደርግ ይሆን? አይጠበቅም።

ለማንኛውም  ፖሰ‍ተር ታምራትን ለዚህ ሥራው ላመሰግነው እወዳለሁ። አመሰግናለሁ ፓስተር ታምራት! እግዚአብሔር ይስጥህ

እናንተን አድማጭ ተመልካቾቼንም  ስለተከታተላችሁኝ አመሰግናችኋለሁ! እግዚአብሔር ይስጣችሁ።

ሁሉ ቀን መልካም  ቀን ይሁንላችሁ።

የሰማና የወደደ ላልሰማ ያሰማ!

ያየና የወደደ ላላየ ያሳይ

ያነበበና የወደደ ላላነበበ ያስኑብብ

ሰብስክራይብ ፣ሼር፣ ላይክ ደወሏን ይጫኑ እንዲሉ 

ባንቱ ገብረማርያም

ጠ/ሚሩን እግዚአብሄርን አሳዝኗል| ይህ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያዬ ነው ይላል ጌታ| ፓ/ር ታምራት ሕይሌ ለጠ/ሚሩ የተናገሩት ከባድ ትንቢት|


Comments

Popular posts from this blog

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ (1)  ድንግል ማርያምን ስለማክበር (2) ለጥያቄዎች መልስ (ሀ) ድንግሊትን ‘የወይን ግንድ (ተክል)’ና የ ‘ሕይወት በር’ የሚል ማዕረግ  ለምን እንሰጣታለን? (ለ) ወደ ድንግል ማርያም መጸለይ ትክክል ነው ወይ? (3) የድንግል ማርያም ድንግልና ዘላለማዊነት (4) ለተቃራኒ አስተያየቶች መልስ (ሀ) “የመጀመሪያ ልጇን” የሚለው ሐረግ (ለ) “ሚስትህ” የሚለው ሐረግ (ሐ) “አብረው ከመሆናቸው በፊት ጸንሳ ተገኘች” (መ) “የመጀመሪያ ልጇን እስክትወልድ አላወቃትም” (ሠ)  “ወንድሞቹ” የሚለው ሐረግ   የቅድስት ድንግል ማርያም  ክብሯ (1) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ድንግል እመቤታችንን አያከብሩም፤ ደግሞም እንድታማልድላቸውም (እንድትማልድላቸውም)  አይጠይቋትም።ከእነርሱ ወገኖች አንዳንዶቹ እንዲያውም ጫጩቱ ከተፈለፈለ በኋላ ዋጋ ከሌለው የዶሮ እንቁላል ቅርፊት ጋር እስከሚያመሳስሏት ይደርሳሉ።ይህ የተጋነነ ማቃለል የመጣው ምናልባት ሮሜዋውያን ካቶሊኮች የተጋነነ ማክበር ስለሚያከብሯት ለዛ ተቃርኖ ከማሳየት አዝማሚያ ሊሆን ይችላል። ስለዚህም ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን አንዱንም የእርሷን በዓል አያከብሩም።  (2) አንዳንዶቹ የፕሮቴስታንት ወገኖች ድንግል ማርያምን “እህታችን” ይሏታል። (3) በተጨማሪ አንዳንዶቹ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጌታ ኢየሱስን በድንግልና ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር ጋብቻዋን ፈጽማለች፤ የ‘ኢየሱስ ወንድሞች’  ወይም የ’ጌታ ወንድሞች’ ተብለው የተጠሩ ልጆችን ወልዳለች ይላሉ።  (4) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ቤተክርስቲያናችን ለድንግል እመቤታችን የሰጠቻቸውን አንዳንድ የማዕረግ ስሞችም ይቃወማሉ።  (5) ድንግልን ያለማክበራቸው አንዱ...

Comparative Theology የነገረ መለኮት ንጽጽር (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት)/ በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሲኖዳ ሳልሳዊ

 የነገረ መለኮት ንጽጽር  (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት): የወደደ  ሁሉ በነጻ እንዲጠቀምበት ተፖስቷል። ይሁን እንጂ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ስለሆነ በየትኛውም መልኩ ለንግድ እንዲውል አልተፈቀድም። ልዩ ልዩ መግቢያ የሚለውን መጀመሪያ ካነበቡ በኋላ የተቀረውን በተመረጠው ቅደም ተከተል ማንበብ ይቻላል። ልዩ ልዩ መግቢያ   ጥምቀት   ትውፊት (ወግና ልማድ)   መካከለኝነት   ጾም የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ   ሥርዐት ንስሐ

ከቄስ ( ዶ/ር ) ቶሎሳ ይልቅ

 አድማጭ ተመልካቾቼ አንደምን ከረማችሁ? የአብርሃም አምላክና አምላካችን የተመሰገነ ይሁንና እኔ ደህና ነኝ።"ከቄስ (ዶ/ር ) ቶሎሳ ይልቅ" በሚል ርዕስ ያዘጋጀሁትን  የሚከተለውን መልዕክቴን እንድትከታተሉልኝ በታላቅ አክብሮት እጠይቃችኋለሁ። ባንቱ ገብረማርያም ነኝ ከቄስ (ዶ/ር) ቶሎሳ ይልቅ           ቄስ (ፓስተር) ዶ/ር ቶሎሳ  ጉዲና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን በአትላንታ/ጆርጂያ ፓስተር መሆናቸው በብዙዎች ዘንድ የሚታወቅ ይመስለኛል። በበኩሌ የማከብራቸውም ሰው ናቸው። በወንጌላውያን መኻል ለበርካታ ዐመታት ለኢትዮጵያ ሰላምና አንድነት የተናገሩ፣ ያሳሰቡና የጸለዩ መሆናቸውን ሰምቼአለሁ።በነገዳቸው የተደራጁትን የወንዛቸው ልጆችን ወቀሳ ተቋቁመው ለመላው ኢትዮጵያዊ ሲጮኹ የኖሩ ናቸው።           ስለ እሬቻ የሰጡት ትምህርት እስከዛሬ እንደሞዴል የማየው ነው። እሬቻን እንዳይከተሉና እንዳያስፋፉ የአሁኖቹን የመንግሥት ዐላፊዎች የመከሩበትንም ጊዜ አስታውሳለሁ።ዛሬም ይኸንኑ ለማድረግ አልታከቱም።           የወንጌላውያን ሽማግሌ ብቻ ሳይሆኑ በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ የአገር ሽማግሌ አድርጌ አያቸዋለሁ። ይህን መደላድል የማስቀምጠው ስለእርሳቸው ያለኝን አስተያየት ለማስታወቅና ይኸው ሐሳቤ የጸና መሆኑን ለማስጮህ ነው።አስተያየቴን አልጠየቁኝም፣ የሚጨምርላቸውም ሆነ የሚቀንስባቸው ነገር እንደማይኖርም ጠንቅቄ አውቃለሁ። መደላድሉን አስቀድሜ  ማስቀመጤ ወንድሞችንና እህቶችን “አይዟችሁ አትደንግጡ...