“የአቤል ደም” እና “አብረን ሰው እንሁን” መግቢያ የ“አቤል ደም” ጸሐፊ አባ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ሲሆኑ ፤ የ”አብረን ሰው እንሁን” ጸሐፊ ደግሞ ሰለሞን ጥላሁን (ፓስተር) የኢትዮጵያ ወንጌል አማኝ ነው። የ"አቤል ደም" በእጄ የገባው በመሸጪያ ድንኳኑ ፊት ለፊት ሰልፍ አይቼ ፣ “ምን ቢሆን ነው” በማለት ሰልፉን ተቀላቅዬ ነው (በአትላንታው በአሜሪካ የኢትዮጵያውያን እስፖርትና ባህል በዐል ላይ ማለት ነው)።“አብረን ሰው እንሁን”ን ያገኘሁት አንድ ወዳጄ ልኮልኝ ነው (በዚህ አጋጣሚ ፓስተር ሰለሞንን አንድ ቅጂ ደርሶኛል አመሰግናለሁ ማለት እወዳለሁ)። የአቤል ድምጽ እጄ ከመግባቱ ከሁለት ሳምንት ቀደም ብዬ “አብረን ሰው እንሁን”ን አንብቤው ነበር። የጽሑፌ ርዕስ ይኸንኑ የንባቤን ቅደም ተከተል (ከፊት ወደ ኋላ) የሚያንጸባርቅ ነው። የመጽሐፍ ሐያሲ አይደለሁም። የምጽፈው ለማሔስ አይደለም፣ የተጻፈው ሁሉ ገብቶኛል፣ ዘልቄዋለሁ ብዬም አይደለም።ለወገኑና ለአገሩ ችግር መፍትሔ ተገኘ ብሎ ሰፍ እንዳለ ሰው በ"ፈጣን ንባቤ" ከመጽሐፎቹ የጨበጥኩትን ያህልና የተሰማኝን ለማካፈል ነው። በሳትሁትና በተሳሳትሁት ለመታረምና ለመማር ዝግጁ ነኝ ከመጽሐፍቱ የተማርኩት ሁለቱም መጽሐፎች በርካታ ገጾች በመያዛቸውና ዐሳቦቹም ለእኔ አዲስ በመሆናቸው በማነብበት ወቅት በማስመር፣ በማድመቅ፣ በማክበብና በጥያቄ ምልክት ሞልቼአቸዋለሁ። ያለጥርጥር እጅግ ብዙ የተደከመባቸው ናቸው።በንባቤ እንደተረዳሁት ከሆነ ሁለቱም ጸሐፊዎች “እኛን ኢትዮጵያውያንን ሰው እንሁን” ...