Skip to main content

እኔም ለሄቨን

 

እኔም ለሄቨን
በወገኖቻችን ሕጻናትና ሴቶቻችን ላይ የሚፈጸመው ወሲባዊ ወንጀል “ምነው ኖረ? እንዴትስ ይቆም ይሆን?” በማለት ለብቻዬ ሳወጣና ሳወርድ የኖርኩት ጉዳይ ነው። ባሕላችን ይኸንን ጉዳይ የሚጠየፍ አድርጌ ስለምቆጥር ፤ ወንጀሉን የሚፈጽሙት የአገሬ ልጆች “ይኸንን ባሕል እንዴት ጣሱት? እኩይ ጠባዩንስ ከየት አመጡት? ምን ነካቸው?” ስልም ቆይቼአለሁ።በሄቨን ላይ የሆነው ጉዳይ ግን ድርብርብ ወንጀል ሆኖ ተሰምቶኛል። ከማኅበራዊ መገናኛ እንደተከታተልኩትም ታላቅና ተገቢ ቁጣን ቀስቅሷል። በተለይ ለፍትሕ ያለው ጩኸት እጅግ በግልጽ ይሰማል። ለቤተሰቧም የሃዘኔታ መልዕክት ጎርፏል። በቀጥታ ሄቨንን የተመለከተ ጉዳይ  ደግሞ አንድ ዘፈን በቴዲ አፍሮ ተዘፍኖ ሰምቼአለሁ።ድምጻዊት ቬሮኒካም (ዘፈን ሠፈር ስለማልውል አላውቃትም ነበር) በሄቨን ላይ በተፈጸመው ግፍ ምክንያት አልበሟ የሚወጣበትን ግዜ አራዝማለች።እኔ ያልደረስኩበት ሌላም ነገር ተደርጎ ሊሆን ይችላል።ይህ ሁሉ ሄቨንን ለማስታወስ መልካም ጅማሬ ነው። ነገር ግን የአሁኑን የሕዝብ ቁጣ ወደ ገምቢ ኃይልነት መለወጥ ይገባል እላለሁ። "በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ወሲባዊ ወንጀል ለተፈጸመባቸው ሁለ ፈዋሽ የሆነና ለወደፊቱም ወሲባዊ ወንጀልን ለመከላከል የሚያስችል መንግሥታዊ ያልሆነ እንቅስቃሴ በስሟ ቢጀመር ስሟ ለዘላቂ በረከት ይሆናል። አሁን የታየው ቁጣም  ወደ ጠቃሚ ኃይልነት ይለወጣል። የእርሷ ጉዳይ የአንድ ሰሞን መጯጯህ ብቻ ሆኖም አይቀርም። እንዲህ ዐይነቱ ነገር በእነርሱ ቢዘጋጅ ይሰምራልና ተጽዕኖ ፈጣሬ የሆኑ ግለሰቦች እባካቸው ተባብረው ይኸንን ዐይነት መንግሥታዊ ያልሆነ እንቅስቅሴን ያፍጥኑ" እላለሁ። ይቅርታ! ብቻ ለአዋቂ አይነግሩም፣ ለአንበሳ አይመትሩም። 

Comments

Popular posts from this blog

Comparative Theology የነገረ መለኮት ንጽጽር (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት)/ በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሲኖዳ ሳልሳዊ

 የነገረ መለኮት ንጽጽር  (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት): የወደደ  ሁሉ በነጻ እንዲጠቀምበት ተፖስቷል። ይሁን እንጂ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ስለሆነ በየትኛውም መልኩ ለንግድ እንዲውል አልተፈቀድም። ልዩ ልዩ መግቢያ የሚለውን መጀመሪያ ካነበቡ በኋላ የተቀረውን በተመረጠው ቅደም ተከተል ማንበብ ይቻላል። ልዩ ልዩ መግቢያ   ጥምቀት   ትውፊት (ወግና ልማድ)   መካከለኝነት   ጾም የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ   ሥርዐት ንስሐ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ (1)  ድንግል ማርያምን ስለማክበር (2) ለጥያቄዎች መልስ (ሀ) ድንግሊትን ‘የወይን ግንድ (ተክል)’ና የ ‘ሕይወት በር’ የሚል ማዕረግ  ለምን እንሰጣታለን? (ለ) ወደ ድንግል ማርያም መጸለይ ትክክል ነው ወይ? (3) የድንግል ማርያም ድንግልና ዘላለማዊነት (4) ለተቃራኒ አስተያየቶች መልስ (ሀ) “የመጀመሪያ ልጇን” የሚለው ሐረግ (ለ) “ሚስትህ” የሚለው ሐረግ (ሐ) “አብረው ከመሆናቸው በፊት ጸንሳ ተገኘች” (መ) “የመጀመሪያ ልጇን እስክትወልድ አላወቃትም” (ሠ)  “ወንድሞቹ” የሚለው ሐረግ   የቅድስት ድንግል ማርያም  ክብሯ (1) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ድንግል እመቤታችንን አያከብሩም፤ ደግሞም እንድታማልድላቸውም (እንድትማልድላቸውም)  አይጠይቋትም።ከእነርሱ ወገኖች አንዳንዶቹ እንዲያውም ጫጩቱ ከተፈለፈለ በኋላ ዋጋ ከሌለው የዶሮ እንቁላል ቅርፊት ጋር እስከሚያመሳስሏት ይደርሳሉ።ይህ የተጋነነ ማቃለል የመጣው ምናልባት ሮሜዋውያን ካቶሊኮች የተጋነነ ማክበር ስለሚያከብሯት ለዛ ተቃርኖ ከማሳየት አዝማሚያ ሊሆን ይችላል። ስለዚህም ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን አንዱንም የእርሷን በዓል አያከብሩም።  (2) አንዳንዶቹ የፕሮቴስታንት ወገኖች ድንግል ማርያምን “እህታችን” ይሏታል። (3) በተጨማሪ አንዳንዶቹ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጌታ ኢየሱስን በድንግልና ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር ጋብቻዋን ፈጽማለች፤ የ‘ኢየሱስ ወንድሞች’  ወይም የ’ጌታ ወንድሞች’ ተብለው የተጠሩ ልጆችን ወልዳለች ይላሉ።  (4) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ቤተክርስቲያናችን ለድንግል እመቤታችን የሰጠቻቸውን አንዳንድ የማዕረግ ስሞችም ይቃወማሉ።  (5) ድንግልን ያለማክበራቸው አንዱ...

ስለ "አስታዋሽ ጾምና በዐሉ" ጥያቄና መልስ

 ስለ "አስታዋሽ ጾምና በዐሉ" ጥያቄና መልስ  ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ፦ ሕልውናችንን-ነጻነትችንን የማረጋገጥና የማስቀጠል አንድነታችንን የመጠበቅና የማጠንከር  በእሴቶቻችን የመደሰት፣ እነርሱን የመንከባከብና የማስተዋወቅ  በረከታችንን የማብዛትና የማካፈል  ኃላፊነቶቻችንን በማኅበር ፣ በማስተዋልና በትጋት እንድንወጣ “ጾሙና በዐሉ" አስታዋሽ ባሕላዊ ምልክታችን ይሁንልን   ጥያቄ 1 ፡ አድማጭ ተመልካቾቻችን እንኳን ደህና መጣችሁ።የከበረ ሰላምታችን ይድረሳችሁ። ዛሬ የምንወያየው ከአቶ ባንቱ ገብረማርያም ጋር ይሆናል። አቶ ባንቱ በሙያው ፋርማሲት ነው። እንደነገረኝ በእምነቱ ደግሞ ባፕቲስት ነው።ለዐማራ ሕዝብና ዎገኖቹ ባሕላዊ ምልክት የሚሆን “ጾምና በዐልን” በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል። የምንወያየውም ስለዚሁ "ጾሙና በዐሉ" ምልክትነት ይሆናል።  አቶ ባንቱ ለመወያየት  ወደ እኛ በመምጣትህ አመሰግንሃለሁ። እንኳን ደህና መጣህ። አንተ እያልኩ ልቀጥል ወይስ አንቱ? መልስ 1፡ ዎገኔ፡   እንኳን ደህና ቆየኸኝ። ለአድማጭ ተመልካቾቻችሁም ሰላምታዬ ይድረስልኝ። አንተ በለኝ። የሚያውቀኝ ሁሉ አንተ ነው የሚለኝ።  ጥያቄ 2 ፡ እሺ  አንተ እያልኩ እቀጥላለሁ። አቶ ባንቱ፣ ምናልባትም ብዙ ሰው ስለማያውቅህ  እስቲ ስለራስህ በአጭሩ ንገረን። ወዲያውም መክፈቻ ይሆነናል መልስ 2 ዎገኔ ፦ አስቀድሜ ይኸን ዕድል ስለሰጠኸኝ ላመሰግንህ እወዳለሁ። አድማጭ ተመልካቾችህንም ጊዜ ወስደው  ውይይቱን  ስለሚከታተሉ ላመሰግናቸው እወዳለሁ።አዎን፣ ባንቱ ገብረማርያም እባላለሁ።እንደነገሩኝ የተወለድኩት ሽርካ በዛሬ አጠራሩ በአርሲ ዞን ነው።ነፍስ ያወቅሁትና ትምህርት ...