Skip to main content

የተሸፋፈነው እውነት ይገላለጥ


የተሸፋፈነው እውነት ይገላለጥ

አስቴር  በዳኔ በ“ሀሌታ” ቃለመልልሷ ውስጥ ሶስት ዋና መልዕክቶችን ታቀርባለች።

መጀመሪያ፣ “አሁን ትልልቅ ጦርነቶችን ያስነሳው ነገር…” በማለት የጦርነቱን እውነተኛ መነሻ ትደብቃለች።

ሁለተኛ፣ “የሆነ ብሔረሰብና የሆነ ሃይማኖት የአገር ባለቤት ነኝ ብሎ ተቀምጧል” በማለት ተጠቂውን እንደ አጥቂ ታቀርባለች፣ እውነቱን ታዛባለች።

ሶስተኛ፣ “ቶለሬት የማያደርግ ትውልድ…” በማለት ስለተጠቂዎቹ መከራ ኀላፊነቱን በሃሳቧ ለፈጠረችው ማኅበረሰብ ትሰጣለች፤ መንግሥትን ግን ነጸ ታደርገዋለች።

እነዚህ መልዕክቶች በአንድ አቅጣጫ ያዘምማሉ፤ የጦርነቱን መነሻ፣ የተጎጂዎችን መከራ፣ የመንግሥትን ኃላፊነት — ይሸፋፍናሉ።

የተዘጋጀው መጋረጃ

አስቴር የተናገረችው እውነት አይደለም። በአማራዎች ላይ የተጀመረውን ጦርነት ለመሸፋፈን የተቀመጠ መጋረጃ ነው።

እውነቱን አላቀረበችም፤ ቀበረችው እንጂ። ስለ ተጠቂዎቹ ጉዳት አልተነፈሰችም። የተጎጂዎቹንና የጎጂዎቹን ሥፍራ አቀያይራለች። ተጠያቂዎቹን አላጋለጠችም፤ ሸፋፈነቻቸው።

ጦርነቱን ያወጀው መንግሥት ነው። መልዕክቷ ያን እውነት ተደብስብሶ እንዲያልፍ የታለመ ነው። ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን ባለመጠበቁ መንግሥትን እንዳይጠየቅም የሚሰውር  ነው።

እውነቱን በመደበቅ ብቻ አላቆመችም፤ ቅሬታን የሚያባብስ፣ የመበቃቀል አዙሪትን የሚጭር ሃሳብ ተክላለች።

ይህንን የተሸፋፈነውን መልዕክቷን ገላልጦ ማየት —አደገኛነቱንም መመልከት ያስፈልጋል። አዎ — የተሸፋፈነው ይገላለጥ!

እርሷም ስህተቷን ታርም — መንግሥትን ተጠያቂ ታድርግ!

----------------------------------------

የጸሀፊ ማስታወሻ

በእህቴ አስቴር ላይ የግል ጥላቻ የለኝም። ይህ ጽሁፍ የሚመለከተው የእርሷን ፖለቲካዊ ምልከታዋንና  የንግግር ምርጫዋን ነው፤ የግል ስብዕናዋን አይነካም።

See Through the Smoke

Aster’s words are not truth — they are a shield placed to cover the government that launched the war on Amharas. She did not present the truth; she buried it. She did not acknowledge the victims; she inverted them. She did not expose power; she concealed it.

The government is the one that declared the war. Her message is crafted to hide that fact behind a cloud of misdirection. It also shields the government from accountability for failing to protect Orthodox Christians.

She didn’t just mask the truth — she introduced a rhetoric that fuels grievance and a cycle of revenge. She didn’t present the political reality; she blurred the cause in a way that feeds the very cycle her framing ignites.

See through the smoke.

May she correct her error — and hold the government accountable.

----------------------------------------

Author’s Note

I hold no personal animosity toward sister Aster. My critique addresses the political framing and rhetorical choices in her message, not her dignity as an individual.



Comments

Popular posts from this blog

ጥምቀት

  ጥምቀት       (1) የጥምቀት ፍቱንነቱ (2) ማጥመቅ የካህን ተግባር ነው (3) የጥምቀት አስፈላጊነቱ (4) ጥምቀት በመንከር (በመጥለቅ) (5) የልጆች (የሕጻናት) ጥምቀትሳቦች (6) ተቃውሞዎች   ጥምቀት   በእኛ በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንቶች መኻል ጥምቀትን በተመለከተ ያሉት ልዩነቶች የጥምቀትን ትምህርት በአምስት ጉልህ   ፍሬ ነገሮች ሥር አጠቃሎ መነጋገር ይቻላል። (1)     የጥምቀት   አስፈላጊነቱ   ምንድነው? ፍቱንነቶቹስ (ጠቀሜታዎቹስ) ምንድናቸው? ኦርቶዶክስ ጥምቀት ‘ድኅነት’ን፣ ‘መንጻት’ን፣ ‘መጽደቅ’ን፣ የ‘ሕይወት መታደስ’ን እና በ’ክርስቶስ አካል አባል’ መሆን’ን መቀበያ መንገድ ነው ብላ ታምናለች። የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች እንደሚሉት እነዚህን   መቀበያው “እምነት” ብቻ ነው። በ እምነት ብቻ መሆኑ ትክክል ከሆነ ታዲያ የጥምቀት አስፈላጊነቱ ምኑ ላይ ነው? የክርስትና ምልክት ብቻ መሆኑ ነውን? ወይስ “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው” (ማቴ 28:19-20) የሚለውን የጌታን ትዕዛዝ መታዘዝ ብቻ መሆኑ ነው? (2 ) ማነው ማጥመቅ ያለበት? በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጥምቀት የሚከናወነው በካህን ብቻ ነው። ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ግን የሰውን ክህነት ጨርሶ አይቀበሉም። ስለሆነም በእነርሱ ቤተ ክርስቲያን የሚያጠምቀው ካህን ወይም ቄስ ያልሆነ አገልጋይ ነው።   ይህ አገልጋይ የቤተክርስቲያኒቷ ሽማግሌ ወይም ሴት ሽማግሌ (የሴቶችን ሽምግልና ...

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ

የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ (1)  ድንግል ማርያምን ስለማክበር (2) ለጥያቄዎች መልስ (ሀ) ድንግሊትን ‘የወይን ግንድ (ተክል)’ና የ ‘ሕይወት በር’ የሚል ማዕረግ  ለምን እንሰጣታለን? (ለ) ወደ ድንግል ማርያም መጸለይ ትክክል ነው ወይ? (3) የድንግል ማርያም ድንግልና ዘላለማዊነት (4) ለተቃራኒ አስተያየቶች መልስ (ሀ) “የመጀመሪያ ልጇን” የሚለው ሐረግ (ለ) “ሚስትህ” የሚለው ሐረግ (ሐ) “አብረው ከመሆናቸው በፊት ጸንሳ ተገኘች” (መ) “የመጀመሪያ ልጇን እስክትወልድ አላወቃትም” (ሠ)  “ወንድሞቹ” የሚለው ሐረግ   የቅድስት ድንግል ማርያም  ክብሯ (1) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ድንግል እመቤታችንን አያከብሩም፤ ደግሞም እንድታማልድላቸውም (እንድትማልድላቸውም)  አይጠይቋትም።ከእነርሱ ወገኖች አንዳንዶቹ እንዲያውም ጫጩቱ ከተፈለፈለ በኋላ ዋጋ ከሌለው የዶሮ እንቁላል ቅርፊት ጋር እስከሚያመሳስሏት ይደርሳሉ።ይህ የተጋነነ ማቃለል የመጣው ምናልባት ሮሜዋውያን ካቶሊኮች የተጋነነ ማክበር ስለሚያከብሯት ለዛ ተቃርኖ ከማሳየት አዝማሚያ ሊሆን ይችላል። ስለዚህም ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን አንዱንም የእርሷን በዓል አያከብሩም።  (2) አንዳንዶቹ የፕሮቴስታንት ወገኖች ድንግል ማርያምን “እህታችን” ይሏታል። (3) በተጨማሪ አንዳንዶቹ ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ጌታ ኢየሱስን በድንግልና ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር ጋብቻዋን ፈጽማለች፤ የ‘ኢየሱስ ወንድሞች’  ወይም የ’ጌታ ወንድሞች’ ተብለው የተጠሩ ልጆችን ወልዳለች ይላሉ።  (4) ፕሮቴስታንት ወንድሞቻችን ቤተክርስቲያናችን ለድንግል እመቤታችን የሰጠቻቸውን አንዳንድ የማዕረግ ስሞችም ይቃወማሉ።  (5) ድንግልን ያለማክበራቸው አንዱ...

Comparative Theology የነገረ መለኮት ንጽጽር (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት)/ በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ሲኖዳ ሳልሳዊ

 የነገረ መለኮት ንጽጽር  (በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት): የወደደ  ሁሉ በነጻ እንዲጠቀምበት ተፖስቷል። ይሁን እንጂ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ስለሆነ በየትኛውም መልኩ ለንግድ እንዲውል አልተፈቀድም። ልዩ ልዩ መግቢያ የሚለውን መጀመሪያ ካነበቡ በኋላ የተቀረውን በተመረጠው ቅደም ተከተል ማንበብ ይቻላል። ልዩ ልዩ መግቢያ   ጥምቀት   ትውፊት (ወግና ልማድ)   መካከለኝነት   ጾም የድንግል ማርያም ክብሯና ዘላለማዊ ድንግልናዋ መንፈሳዊ ስጦታዎችና በልሳኖች የመናገር ስጦታ   ሥርዐት ንስሐ