በሕይወቱ ሊበረታ ነው ምኞቱ
ዶ/ር ደረጀ ከበደ በመዝሙር አገልግሎቱ የነበረበትን ፈተና ተናገረ። ይሁን እንጂ እርሱ በመዝሙሩ በታወቀበት ዘመን የአገልጋዮች ሕይወት ለአደባባይ የተገለጠ ነበር። በጊዜው ከሌሎች ዋንኞቻችን የተለየ ነቀፋ ቢኖርበት ኖሮ የመታወቅ እድል ነበረው።ለማንኛውም የውስጥ ትግሉን ከራሱ በላይ የሚያውቅ የለምና "እንደ ዘመርኩት አልኖርኩም" ያለውን እንዳለው እቀበለዋለሁ።
ዘፈንን በተመለከተ በዚያው ወደ ዘማሪነት በመጣበት ዘመን "ዘፋኝነት ኃጢአት ነው፣ ዘፈን የሥጋ ሥራ ነው" ብሎ ማመን ጤናማ ትምሀርት ነበር። ጆሮዬ ሳያጣራ ቀርቶ ካልሆነ በስተቀር አብዮታዊ መዝሙር አልዘምርም (ያው ዘፈን መሆኑ አይደል) በማለት መከራን ተቀብሏል። አሁንም በዩትዩቡ የዱሮውን የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም እንደሚያነብ አሳይቶናል። ዛሬም ዘፋኝነት ኃጢአት ነው የሚል ፊት ለፊቱ አለ።ስለዚህ ዘፈንን ስለማዳመጥ በወንጌል አማኞች ዘንድ የሰፈነውን ሐሳብ ያውቃል ብል ያልሆነ ነገር በእርሱ ላይ መለጠፍ አይሆንብኝም።
ታዲያ የቴዲ አፍሮ ‘ኢቶሪካ’ ዘፈንን ማዳመጡ ከምን የተነሳ ነው?
እንዳለው እንደዘመረው አለመኖሩ ይሆን? የወንድሜን የዮናስ ጎርፌን ሙግት ገዝቶ ይሆን? ለነገሩ አዲሱ የመጽሐፍ ትርጉምም ዘፈንን እንደ ቀድሞው ትርጉም አይገልጠውም።የተለየ ትንተና (commentary) እየተሰጠበትም ይገኛል። ይህ ተጽእኖ አሳድሮበት ይሆን? ነው ወይስ “እስቲ ቴዲ አፍሮ ምን ብሎ ዘፍኖ ይሆን?” ብሎ በመጓጓት አደመጠው? ለእነዚህ ጥያቄዎች መልሱ ያለው በወንድሜ ደረጀ እጅ ነው።
ዘፈኑን ያደመጠው ግን አስቦበት መሆኑ ድብቅ አይደለም።ዘፈን ጽድቅ ነውና አዳምጡ ብሎ አልሰበከንም (ዘፈኑን ‘ወንጌል ነው ስላለው’ በሌላ ክፍል (ንዑስ ርዕስ) የማነሳው ይሆናል።
መዝሙሩና ሥራው አልገጠመም ብሎ ካሳሰበው የራሱ ፓስተር ቀርቦ ሊማከረው፣ ሊጸልይለትና ሊረዳው ይችላል—-በሕይወቱ እንዲበረታ። ያም ሆኖ ከማኀበራዊ መገናኛ እንደሚታየው ያሰቡለት፣ ያዘኑለት ያዘኑበትም እጅግ ብዙ ነፍሳት አግኝቷል።
እኔ ደግሞ ስለ ሕይወቱ ከመመስከሩና ዘፈን ከማዳመጡ ያገኘነው ትርፍ ወይም በጎ ነገር አለ ባይ ነኝ።
እርሱ እንዳደረገው የክርስትና ሕይወታችንን እንድንመረመርና የምናድግበትን እንድናይ ምክንያት ሆኖናል።
በአስጨናቂዎቻቸው መዳፍ ሥር በወደቁ ወገኖች በተለይም በአማራው ላይ ስለሚደርሰው ግፍ ትኩረታችን ተጨምድዶ እንዲያዝ አድርጓል (በአማራ ስለደረሰው ግፍ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ሪፖርቶች ክፍል 1 የግርጌ ማስታወሻ ይመልከቱ)።
ዶ/ር ደረጀ የእነርሱ ወገን ባለመሆኑ ያዘኑና የተቆጡ መኖራቸውን አይተንበታል (እንደ ራሴ በማየት ህመማቸውን እረዳለሁ)።
ባንቱ ገብረመሸርያም
ከአዎን ድምጽ
- ግፉ በአማራ ላይ (መግቢያ)“ግፉ ሲበዛ ፣ አፍ ሁሉ ሲዘጋ ፣ ያኔ ነቢያዊ ድምጽ ይገኝ ፡ ክፍል 1
- በሕይወቱ ሊበረታ ነው ምኞቱበሕይወቱ ሊበረታ ነው ምኞቱ
- የተለወጠ ክርስቲያን ንግግር ነው?የተለወጠ ክርስቲያን ንግግር ነው?
- ከተደራጁ ሃይማኖቶች እንውጣን?ከተደራጁ ሃይማኖቶች እንውጣን?
- በእውኑ ካውንስሉ ፖለቲካ ይሠራልን?በእውኑ ካውንስሉ ፖለቲካ ይሠራልን?
- ፌክ ኢትዮጵያኒስቶች ከፊቱ ዞር በሉፌክ ኢትዮዽያኒሰቶች ከፊቱ ዞር በሉ!
- ቴዲ አፍሮ መጥምቁ ዮሐንስ ነው?ቴዲ አፍሮ መጥምቁ ዮሐንስ ነው?
- ዘፈኑን ወንጌል አለው! አልሳተም?ዘፈኑን እኮ ወንጌል አለው? አልሳተም ትላላችሁ?
- ነቢያዊ ድምጽ (መደምደሚያም) ነቢያዊ ድምጽ /መደምደሚያ
Comments
Post a Comment