ዘፈኑን እኮ ወንጌል አለው? አልሳተም ትላላችሁ?
ዘፈኑን “ወንጌል ነው” ማለቱ መሳት አይደለም። የተቃወሙት ሰዎች ዶክተሩ ዘፈኑን ወንጌል አደረገ ብለው ነው የተረዱት። እኔ ግን እንዲህ እላለሁ፦
“ማኀበራዊ ወንጌል”
1
የሚለውን አጠራር ዛሬ እጅግም አንጠቀምበትም። ምክንያቱም ከስሙ ጋር የሚነሱ ያልተፈለጉ ክርከሮችን ለማስቀረት ነው። ይሁን እንጂ እንደ በርካታ የፕሮቴስታንት አሰተማሪዎች ወንጌልን ከማህበራዊ ፍትሕ መነጠል አይቻልም።
የተራራው ስብከትም ይሁን የመጥምቁ ዮሐንስ የ“ንስሐ ግቡ” መልዕክትም በግልጽ ሁኔታ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ግንኙነታዊ ፍትሕን የሚያስተምር መሆኑን የፕሮቴስታንት አስተማሪዎች ያስረዳሉ
2።
ይህንን አመለካከት በመቀበል የኢየሱስ ትምህርት በግል ሕይወት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን በማህበራዊ ፍትሕ ላይም ግልጽ ጥሪ እንደሚያቀርብ መመልከት ይቻላል።
በእርግጥ ይህን የማይቀበሉ ሌሎች የተከበሩ አስተማሪዎችም አሉ፣ ግን ሁለቱም ወንጌልን ከፍትሕ አያፋቱትም
3።
ስለዚህ እውነት፣ ወይም ፍትሕ ወይም ትክክለኛው ሞራል በወንጌል መሰል ዘፈን ቢገለጥ የአግዚአብሔር መልዕክትነቱ አይለወጥም። የወንጌል የሆነው መልዕክት ከቤተክርስቲያን ውጭ ባሉ ሰዎች ሲነገር ያ የአግዚአብሔርን እውነት የሚያስታውሰን ነው
4።
የቴዎድሮስ ካሣሁንን ዘፈን ወንጌል ነው ብሎ ደረጀ ሲናገር በዘፈኑ የተላለፈው የፍትሕ፣ የፍቅርና የመሳሰሉት መልዕክት የወንጌል አካል ናቸው ማለቱ ሆኖ ይታየኛል። እንግዳ ነገር እንደተናገረ ያህል የሚያስፈራ አይደለም። የግል ድኅነትን ጉዳይ እንዳይውጠው መጠንቀቁ ግን ክፋት የለውም።
ግን ግን ይኸንን ሰበብ አድርጎ “የአማራ ሕዝብ ሰቆቃ ይቁም” የሚለውን ድምጽ ማፈን ጨካኝነት አይሆንም?
ባንቱ ገብረማርያም
ከአዎን ድምጽ
- ግፉ በአማራ ላይ (መግቢያ)“ግፉ ሲበዛ ፣ አፍ ሁሉ ሲዘጋ ፣ ያኔ ነቢያዊ ድምጽ ይገኝ ፡ ክፍል 1
- በሕይወቱ ሊበረታ ነው ምኞቱበሕይወቱ ሊበረታ ነው ምኞቱ
- የተለወጠ ክርስቲያን ንግግር ነው?የተለወጠ ክርስቲያን ንግግር ነው?
- ከተደራጁ ሃይማኖቶች እንውጣን?ከተደራጁ ሃይማኖቶች እንውጣን?
- በእውኑ ካውንስሉ ፖለቲካ ይሠራልን?በእውኑ ካውንስሉ ፖለቲካ ይሠራልን?
- ፌክ ኢትዮጵያኒስቶች ከፊቱ ዞር በሉፌክ ኢትዮዽያኒሰቶች ከፊቱ ዞር በሉ!
- ቴዲ አፍሮ መጥምቁ ዮሐንስ ነው?ቴዲ አፍሮ መጥምቁ ዮሐንስ ነው?
- ዘፈኑን ወንጌል አለው! አልሳተም?ዘፈኑን እኮ ወንጌል አለው? አልሳተም ትላላችሁ?
- ነቢያዊ ድምጽ (መደምደሚያም) ነቢያዊ ድምጽ /መደምደሚያ
- የማህበራዊ ወንጌል ክርስቲያኖች የመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ-ምግባርን ሥራ ላይ በማዋል ድህነት፣ እኩልነት መታጣትን፣ የሠራተኛ ብዝበዛን የመሳሰሉትን ማኅበራዊ ችግሮች ስለመፍታት የሚያስተምር ነው። ዐላማውም በምድር ላይ “የእግዚአብሔር መንግሥት” መገንባት ነው። ትኩረታቸውን ማህበራዊ ፍትህ ላይ ባደረጉ ልዩ ልዩ አገልግሎቶች (ሚኒስትሪዎች) ውስጥ እሴቶቹ ዛሬም ድረስ ተፅዕኖ አላቸው። •Christopher H. Evans, The Social Gospel in American Religion: A History (New York: NYU Press, 2017), 45.
- [FGreen, Wright, Keener, France — የኢየሱስና የመጥምቁ ዮሐንስ መልዕክት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፍትሕን እንደሚያስተምሩ ያሳየሉ
- Social gospe” የሚለውን ቃል ቢቃወሙም በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ፍትሕን እንደ ክርስቲያን ግዴታ የሚቀበሉ ወግ አጥባቂ አስተማሪዎች አሉ። ለምሳሌ ጆን ማካርተር የድኅነት መልዕክት ከማህበራዊ አቀንቃኝነት ጋር እንዳይምታታ በግልጽ “ማኅበራዊ ወንጌልን” ይቃወማል። ያም ሆኖ የፍትሕን አስፈላጊነት ያሰምርበታል። Sources: • John MacArthur, The Gospel According to Jesus (Zondervan, 1994), xiii–xiv. • John MacArthur, “The Social Gospel,” Grace to You (sermon, 2007).
- የእውነት ቃል ከቤተክርስቲያን ውጭ ቢመጣም የእግዚአብሔር ነው ብለው የሚያስተምሩት እነዚህ ናቸው፦ Augustine, On Christian Doctrine (De Doctrina Christiana), II.18.28 (“Wherever truth may be found, it belongs to the Lord.”); John Calvin, Institutes of the Christian Religion, II.2.15–16 (on “common grace,” affirming that God grants truth and moral insight even to unbelievers); John Wesley, Preface to Hymns and Sacred Poems (1739) (“The gospel of Christ knows no religion but social; no holiness but social holiness.”); Dietrich Bonhoeffer, Life Together, ch. 4, and Ethics, “Christ, Reality, and Good” (teaching that God’s truth may confront the church even through voices outside it).
Comments
Post a Comment