ነቢያዊ ድምጽ /መደምደሚያ
የኢትዮጵያውያ ወንጌላውያንም ሆኑ ጴንጤቆስጣዊ አብያተ ክርስቲያናት የወንጌል አገልግሎታቸው በግል መዳን፣ ቅድስና፣ በመከራ መታገስ እና በሰማይ ተስፋ ዙሪያ ያተኮረ ነው። ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፍትህን አያነሳም። ይህ አካሄድ ወንጌልን ከአሜሪካና ከአውሮፓ ካመጡልን ወግ አጥባቂ ሚሲዮናውያን የተወረሰ ነው
1።
ደርግ ሥልጣን ላይ በወጣበት አካባቢ በላቲን አሜሪካ የታየው የሊበሬሽን (ነጻ የመውጣት) ቲዎሎጂ
2
ወደ ኢትዮጵያ አልገባም። ገብቶ ቢሆን ኖሮ በሚሲዮናውያኑ መር ወንጌል አገልግሎቱ ላይ ማህበረሰብን መለወጥ ይታከልበት ነበር ማለት ስህተት አይሆንም። ያንን ያመለጠ እድል አድርጎ ማሰብ ይቻላል።
በዚያኑ ወቅት የቄስ ጉዲና ቱምሳም “ሁለንተናውን ሰው” ማገልገል የሚለው ነገረ መለኮት የምዕራቡ ነገረ መለኮት በኢትዮጵያ ሁኔታ የጎደለውን እንዲያሟላ መንገድ ከፋች ነበር
3። ይሁን እንጂ መካነ ኢየሱስ በወቅቱ ይኸን ለመቀበል ያልተዘጋጀች ስለነበርና ታሪካዊ ሁኔታ ባለማመቸቱ ተጨናግፏል። የባከን እድል ነው ማለት ይቻላል።
በደርግ ዘመን ቤተክርስቲያን ብትሰፋም በሚሲዮኑ ከተተለመው መሥመር አልወጣችም። በሕዝባዊ ጉዳይ መግባት ለሞት የሚያደርስ ስለነበርም ዝምታውን ከመሞት የመሰንበት ዘዴ ሆኗት ነበር
4።
ከደርግ መውደቅ ወዲህም አካባቢው በዛው በግል ድኅነት ዙሪያ ተወስኖ ለመሥራት ነጻነት ይኑር እንጂ በማኅበራዊ ጉዳይ ለመግባት አመቺ ሁኔታም አልነበረም።
በእርግጥ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የሃይማኖት ነጻነቱን በአደባባይ ሳይቀር ፕሮግራም ማድረግ እስከሚቻል ድረስ አስፍተውታል። ታዲያ ምን ያደርጋል እንደ ተቃውሚዎቻቸው ግምገማ ከሆነ ቤተ እምነቶችን መልሰው ካልተቆጣጠርኳችሁ ይላሉ
5።
በካውንስሉ በኩል በማኅበራዊ ጉዳይ ለመሳተፍ ለወንጌል አማኞች በሩን ከፈት ያደረጉትም ይመስላል። ይሁን እንጂ እስካሁን ስለተጨቆኑ ወይም ስለተገፉ ድምጽ የሚያሰሙ ብቅ አላሉም። እኔ እንደ ተከታተልኩት ከሆነ ወንጌላውያኑ ዝምታቸውን አልሰበሩም። ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ የሚባሉትን መገመት ይቻላል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚወራባቸው ልጓም አስገብተው ይሆን? በደርግ ዘመን የነበረው ድንጋጤ አሁንም ድረስ ከሕዝበ ክርስቲያኑን ልብ አልወጣ ይሆን? ወንጌል አማኙ በብልጽግና ወንጌል የግል ስኬትና ምቾት ተስፋ ተሞልቶ የራሱን ጉዳይ ብቻ እያየ ይሆን?ብዙዎቹ አገልጋዮች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀረቤታ አላቸው ይባላል። እርሳቸውን ላለማሳዘን ለጥንቃቄ ይሆን?
እነዚህ ሁሉ መልስ ሊሆኑ ይችላሉ። ግን ያው ሁሉም ግምት ነው። ነገር ግን ስለተበደሉ ወይም ስለተገፉ የሚናገር ድምጽ አልተሰማም። ዛሬም በዛው ሚሲዮን መር አገልግሎት ላይ መወሰን ይታያል።
ግፉ ግን በዝቷል። አንዳንዱን ለመስማት እንኳ ይዘገንናል። ደግነቱ “ግፍ ሲበዛ፣ አፍ ሁሉ ሲዘጋ፣ ያኔ ነቢያዊ ድምጽ (Prophetic Voice)
6
” ይነሳል። ለአማራው ያ ነቢያዊ ድምጽ ዶ/ር ደረጀ ከበደ ሆኖ ተገኝቷል። እጅግ የበዛ ‘አዋኪ ሞገድን’ ሰንጥቆ ኩልል ያለ ድምጹን ስለ ግፉአኑ አማራዎች አሰምቷል። እኛም እንተባበረው።
ይቅርታ ነገር አበዛሁባችሁ።
ሁሉ ቀን ሠናይ ቀን ይሁንላችሁ።
ያነበበና የወደደ ለሌላ ያሰማ–ያስነብብ።
ቸር ሰንብቱልኝ
ባንቱ ገብረማርያም
ከአዎን ድምጽ
Modern AI tools were used to support the preparation of this manuscript.
- ግፉ በአማራ ላይ (መግቢያ)“ግፉ ሲበዛ ፣ አፍ ሁሉ ሲዘጋ ፣ ያኔ ነቢያዊ ድምጽ ይገኝ ፡ ክፍል 1
- በሕይወቱ ሊበረታ ነው ምኞቱበሕይወቱ ሊበረታ ነው ምኞቱ
- የተለወጠ ክርስቲያን ንግግር ነው?የተለወጠ ክርስቲያን ንግግር ነው?
- ከተደራጁ ሃይማኖቶች እንውጣን?ከተደራጁ ሃይማኖቶች እንውጣን?
- በእውኑ ካውንስሉ ፖለቲካ ይሠራልን?በእውኑ ካውንስሉ ፖለቲካ ይሠራልን?
- ፌክ ኢትዮጵያኒስቶች ከፊቱ ዞር በሉፌክ ኢትዮዽያኒሰቶች ከፊቱ ዞር በሉ!
- ቴዲ አፍሮ መጥምቁ ዮሐንስ ነው?ቴዲ አፍሮ መጥምቁ ዮሐንስ ነው?
- ዘፈኑን ወንጌል አለው! አልሳተም?ዘፈኑን እኮ ወንጌል አለው? አልሳተም ትላላችሁ?
- ነቢያዊ ድምጽ (መደምደሚያም) ነቢያዊ ድምጽ /መደምደሚያ
- Øyvind Eide, Revolution and Religion in Ethiopia (Brill, 2000).
- Gustavo Gutiérrez, A Theology of Liberation (Orbis Books, 1973); Leonardo Boff, Liberating Theology (Orbis Books, 1979); CELAM Documents: Medellín (1968), Puebla (1979).
- Jörg Haustein, Historiography of Ethiopian Pentecostalism (2011); Rode Molla, EECMY and Society (2018).
- Jörg Haustein, “Religion and the State in Ethiopia,” Journal of Eastern African Studies (2014).
- Jon Abbink, “Religion in Public Life in Ethiopia,” Africa Spectrum (2020).
-
“Prophetic voice is the moral courage to speak truth on behalf of the oppressed, even when silence is safer.”
This means:
• A prophetic voice is not about predicting the future.
• It is about speaking truth to power.
• It is about defending the oppressed, the poor, the marginalized.
• It requires courage, because speaking out can be dangerous.
• Many people stay silent to protect themselves, but a prophetic voice refuses to be silent.
Comments
Post a Comment